በሲዳማ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የRCFSP ፕሮግራም አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በሲዳማ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የRCFSP ፕሮግራም አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በRCFSP ፕሮግራም ለታቀፉ ወረዳዎች በፕሮግራሙ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ, በ2017 አፈፃፀም እና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ የምክክር መድረክ ከወረዳ አመራርና  ፎካሎች ጋር ስብሰባ (Review meeting) ተደርጓል::

ከእቅድ ዝግጅት ግምገማ በፕሮጀክቱ በታቀፉት ወረዳዎች  እየተሰሩ ያሉትን ፕሮጀክቶች በጥራትና በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዉስጥ  እንዲጠናቀቁ ለማድረግ  ከፕሮጀክት አማካሪዎች እና ኮንትራክተሮች ጋርም ምክክር መደረጉ ተገልጿል::

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቢሮ ኃላፊ እንደገለፁት በወረዳዎች ተገባራዊ እየተደረጉ የሚገኙ የመንገድ እና ድልድይ ስራዎችን በቅርበት በወጣው እስታንዳርድ መነሻ ክትትል በማድረግ ሚናቸዉን እንዲወጡ ተናግረዋል::

በሌላም በኩል ሁሉንም ፕሮጀክቶች ግንባታ እና ጥገናን በተመለከተ ከአማካሪዎች ጋር በመሆን ቁጥጥር በማድረግ የተያዘው በጀት ለተባለለት አላማ እንዲዉ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ ገልጿል::

በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እና የሰባቱም ወረዳ አመራሮች ; አማካሪዎች እንዲሁም የወረዳ ፎካል ባለሙያዎች ተገኝተው ተሳተፉ ሆነዋል::

መስከረም 10/2018 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.