በሲዳማ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የRCFSP ፕሮግራም አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::
በRCFSP ፕሮግራም ለታቀፉ ወረዳዎች በፕሮግራሙ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ, በ2017 አፈፃፀም እና የ2018 ዓ.ም እቅድ ላይ የምክክር መድረክ ከወረዳ አመራርና ፎካሎች ጋር ስብሰባ (Review meeting) ተደርጓል::
ከእቅድ ዝግጅት ግምገማ በፕሮጀክቱ በታቀፉት ወረዳዎች እየተሰሩ ያሉትን ፕሮጀክቶች በጥራትና በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዉስጥ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ከፕሮጀክት አማካሪዎች እና ኮንትራክተሮች ጋርም ምክክር መደረጉ ተገልጿል::
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቢሮ ኃላፊ እንደገለፁት በወረዳዎች ተገባራዊ እየተደረጉ የሚገኙ የመንገድ እና ድልድይ ስራዎችን በቅርበት በወጣው እስታንዳርድ መነሻ ክትትል በማድረግ ሚናቸዉን እንዲወጡ ተናግረዋል::
በሌላም በኩል ሁሉንም ፕሮጀክቶች ግንባታ እና ጥገናን በተመለከተ ከአማካሪዎች ጋር በመሆን ቁጥጥር በማድረግ የተያዘው በጀት ለተባለለት አላማ እንዲዉ ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ ገልጿል::
በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች እና የሰባቱም ወረዳ አመራሮች ; አማካሪዎች እንዲሁም የወረዳ ፎካል ባለሙያዎች ተገኝተው ተሳተፉ ሆነዋል::
መስከረም 10/2018 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
ከሙስናና ብልሹ አሠራር የፀዳና የዘመነ የአመራርና ባለሙያዎች ትጋት ለተቋም ግንባታ ቁልፍ እንደሆነ ተገለፀ::
ለተቋማት የአሠራር ሥርዓትን በመዘርጋት የተሻለ ለውጥ ማስመዝገብ ይገባል።
በመናኸሪያዎች እየተተገበረ ያለው የኢ- ቲኬቲንግ (E-ticket) አገልግሎት የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀለት እንደሆነ ተገለፀ።
በሲዳማ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የRCFSP ፕሮግራም አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::
የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደረገ::