በሲዳማ ክልል የመንገድ ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ::

በሲዳማ ክልል የመንገድ ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ::

በሲዳማ ክልል በሰሜናዊ እና ማዕከላዊ ሲዳማ ዞኖች በቢሮ በኩል ግንባታቸው እየተከናውኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን  በቢሮ ኃላፊ በአቶ ጎሳዬ ጎዳና በተመራው ቡድን ምልከታ ተደርጓል::

በሪካፕ ፕሮግራም በኩል የጥገና ሥራ ተጠቃሎ ሪክክብ የተደረገዉ በጎርቼ ወረድ የሚገኘ የዊጣ ጎርቼ ፕሮጀክት በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለማየት ተችሏል::

በመንገዶች ባለስልጣን በኩል እየተገነባ የሚገኘው የዎላ ጃልዶ ቡሳዋ የ14 ኪሜ ማቴሪያል የመበተን ሥራ በጥሩ ሁኔታ ጥራቱ ተጠብቆ እየተሰራ ይገኛል::

መንገዱ የጎርቼ ሻፋሞ እና የአርቤጎና ወረዳዎችን የሚያገናኝ በመሆኑ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳው ከፍተኛ በመሆኑ ትኩረት ተሰጥተው እየተገነባ ይገኛል::

በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በዎንሾ ወረዳ የጥገና ስራው እየተሰራ የሚገኘው የቦካሶ ዳዋሌ መንገድ ጠጠር የማልበሱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ምልከታ ተደርጓል::

ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በወንዶ ገነት ወረዳ በዩዎ አከባቢ አዲስ እየተከፈተ የሚገኘውን መንገድ የከፈተ እና የአፈር ሥራ እየተሰራ  ያለውን እንቅስቃሴ በምልከታ ወቅት ለማየት ተችሏል::

የመስክ ምልከታ እና የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል::

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ታህሳስ 01/04/2018 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.