በዩራፕ ዘርፍ በተደራጁ በወጣቶች አደረጃጀት 27 ፕሮጀክቶች ጥገና እንደሚደረግ ተገለፀ::
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ በዩራፕ ዘርፍ በተደራጁ በወጣቶች አደረጃጀት 27 ፕሮጀክቶች ጥገና እንደሚደረግ ተገለፀ::
በባልፈው በጀት ዓመት በፕሮጅክት ሥራ አፈፃፀም ግምገማ መነሻ በማድረግ የተሻለ አፈፃፀም ያመጡት ከ72 ማህበራት ዉስጥ 56 ማህበራት ተለይቶ ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተጠቅሷል ::
በተመረጡና የሥራ ዕድል በተፈጠረላቸዉ ወጣቶች በኩል 195.5 ኪሜ መንገድ በ14 ወረዳዎች ጥገና እንደሚደረግ ታውቋል ::
በመጨረሻም ማህበራቱ የሚሰሩትን መንገዶችን በዕጣ እንዲለዩ ተደርጎ የዕለቱ ፕሮግራም ማጠቃለያ ተደርጓል::




