በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጳጉሜ 1 የአገልግሎት ቀን በክልል ደረጃ በሁሉም መናሃሪያዎች ዉስጥ ተከበረ::


በመረሃ ግብሩ ላይ የሲዳማ ክልል የሪኦተ ዓለም እና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ አስፋው ጎኔሶ እንዲሁም የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንትባ ክቡር መኩሪያ ማርሻዬ እንዲሁም የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የማናጅመንት አባላት የትራንስፖርት ማህበራት ተሳፋሪዎች እና አሽከርካሪዎች በተገኙበት የጳጉሜ 1 ቀን የአገልግሎት ቀንን ምክንያት በማድረግ በክልል ደረጃ በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር በአሮጌ መናሃሪያ እየተበረ በሚገኘው ፕሮግራም ላይ የታክስ አግልግሎት ከ12 ሰዓት ጀምሮ ነፃ እንደሆነ እና ሁሉም ተሽከርካሪ በጥንቃቄ አገልግሎት እንዲሰጡ እና በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚደርሰዉን ሞት በጋራ ሁሉም የባለ ድርሻ አካላት መከላከል እንደሚገባ የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ አስፋው ጎኔሶ ግልፆዋል ::
የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ መኩሪያ ማርሻዬ በበኩላቸዉ በዛሬ ዕለት ሁሉም አሽከርካሪዎች የሚሰጡትን አገልግሎት ህዝብን ባማከለ እና በቅንነት እንዲያገለግሉ መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል::
በእለቱ አሽከርካሪዎች, የማስልጠኛ ተቋማት የህግ አስከባሪዎች እንዲሁም ተሳፋሪዎች ቃል መሃላ በመግባት ማጠቃለያ ተደርጓል::
ጳጉሜ 1/2015 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::