የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ::

የመስክ ጉበኝቱ ከቦርጃ ውጅግራ ፕሮጀክት የ5.56 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን የፕሮጀክት ስራዎች ያሉበትን ለማየት ተችሏል:: የመንገዱ ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለማየት ችለናል::

የመንገዱ መገንባት የማልጋ እና የወንዶ ገነት ወረዳን የሚያገናኝ በመሆኑ ለአከባቢው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እጅግ በጣም ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መንገድ እንደሆነ በምልከታ ወቅት ለማረጋገጥ ችለናል:: ለዚህም ፕሮጀክት ሁሉም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የዞን እና ወረዳ አመራሮች በቅርበት ክትትል ማድረግ የሚገባው እንደሆነ ተገልፆዋል::

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአጭር ጊዜ ዉስጥ እስከ ጥር 30/2016 ዓ. ም ድረስ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ የእስታር የሥራ ተቋራጩ አስተባባሪዎች አሳውቋል:: ፕሮጀክቱ በታቀደው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የቢሮ ማናጅመንት አመራሩ በቅርበት ክትትል እንደሚያደርጉ ገልፃዋል::

ጥር 3 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.