በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በመድረኩ የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ የቢሮ ማናጅመንት አባላት እንዲሁም አጠቃላይ የቢሮ ባለሙያዎች ተገኝተዉ ተሳታፊ ሆኗል:: በግምገማ መድረኩም የ6 ወር የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል::

በቀረበው ሪፖርት መነሻ በ6 ወር ዉስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ዘርፎች እና ዳይረክቶሮቶች በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥሉ እና በአፈፃፀማቸው በመካከለኛ ደረጃ ያሉና ወደ ኃላ የቀሩ ዘርፎች እና ዳይረክቶሬቶች በቀጣይ ቀሪ ወራት በጉድለት የተለዩ ጉዳዮች ትኩረት ተሰጥተው እንዲከናወኑ አቅጣጫ ተቀምጧል::

በመጨረሻም በቢሮ ደረጃ የሚከናወኑ ቁልፍ ቁልፍ ተግባራት በሙሉ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዉስጥ በውጤታማነት እንዲከናወኑ ተግባቦት ላይ ተደርሶ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ ተደርጓል::

 ታህሳስ 26 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.