በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በመድረኩ የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ የቢሮ ማናጅመንት አባላት እንዲሁም አጠቃላይ የቢሮ ባለሙያዎች ተገኝተዉ ተሳታፊ ሆኗል:: በግምገማ መድረኩም የ6 ወር የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል::


በቀረበው ሪፖርት መነሻ በ6 ወር ዉስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ዘርፎች እና ዳይረክቶሮቶች በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥሉ እና በአፈፃፀማቸው በመካከለኛ ደረጃ ያሉና ወደ ኃላ የቀሩ ዘርፎች እና ዳይረክቶሬቶች በቀጣይ ቀሪ ወራት በጉድለት የተለዩ ጉዳዮች ትኩረት ተሰጥተው እንዲከናወኑ አቅጣጫ ተቀምጧል::


በመጨረሻም በቢሮ ደረጃ የሚከናወኑ ቁልፍ ቁልፍ ተግባራት በሙሉ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዉስጥ በውጤታማነት እንዲከናወኑ ተግባቦት ላይ ተደርሶ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ ተደርጓል::
ታህሳስ 26 /2016 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::