የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ እና የመንገድ ደህንነት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የንቅናቄ መድረክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማጠቃለያ ተደረገ::

በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ኃላፊ፣ ክቡር አቶ ዘገዬ ሀመሶ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ፣ የዞን ዋና አስተዳደሪዎ እና የፊት አመራሮች፣ የከተማ አስተዳደር እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት ተደርጓል::


በሴክተር ጉባኤው ላይ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከል ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሠነድ እንዲሁም የባለ ሁለት ጎማ ሞተር አደረጃጀት መመሪያ የጉባኤ አጀንዳዎች ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የጉባኤው ተሳታፊዎችም በቢሮ ደረጃ እስከ ታች እየተከናውኑ ያሉትን ተጨባጭ ለዉጥ እያስመዘገቡ የሚገኙ እንደሆነ አንስተው በተለይ ከመንገድ ልማት ሥራዎች አንፃር ከጥራት ጋር ተያይዞና በጊዜ ከማጠናቀቅ አንፃር ትኩረት ይበልጥ እንዲደረግ ተነስቷል::
በሌላም በኩል በመንገድ የትራፊክ አደጋ መከላከል ረገድ እየመጡ ያሉትን ለዉጦችን በማጠናከር የትራፊክ አደጋ እያስከተለ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በጋራ በመቀናጀ መቀነስ እንደሚገባ ተገልፆዋል::
በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ በተነሱ ሃሳቦች ላይ ምላሽ በመስጠት በ ጋራ በመቀናጅት መሥራት ከቻልን በመጨረሻም የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ገልፆዎ በእለቱም ለሴክተር ጉባኤ መሳካት የራሳቸውን ሚና ለተወጡ አካላት የምስጋና እዉቅና ሰርትፊኬት ተሰጥተዉ የእለቱ መድረክ ማጠቃለያ ተደርጓል::
ጥር 17/2016 ዓ.ም
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::