የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ እና የመንገድ ደህንነት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የንቅናቄ መድረክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማካሄድ ተጀመረ::
በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ኃላፊ ፣ ክቡር አቶ ዘገዬ ሀመሶ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ፣ የዞን ዋና አስተዳደሪዎች እና የፊት አመራሮች፣ የከተማ አስተዳደር እና የወረዳና አስተዳዳሪዎች፣ የፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል::
በሴክተር ጉባኤው ላይ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት፥ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከል ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሠነድ እንዲሁም የባለ ሁለት ጎማ ሞተር አደረጃጀት መመሪያ አጀንዳዎች ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል::
ጥር 17 /2016 ዓ.ም




