ከሙስናና ብልሹ አሠራር የፀዳና የዘመነ የአመራርና ባለሙያዎች ትጋት ለተቋም ግንባታ ቁልፍ እንደሆነ ተገለፀ::

ከሙስናና ብልሹ አሠራር የፀዳና የዘመነ የአመራርና ባለሙያዎች ትጋት ለተቋም ግንባታ ቁልፍ እንደሆነ ተገለፀ::

ለሴክተሩ ተቋማት አመራርና ባለሙያዎች  የአቅም ግንባታ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደዋል።

 ቢሮ ሀላፊው ሲናገሩ :- የቢሯችን አመራርና ባለሙያዎች ከብልሹ አሠራርና የሠራተኞችን አዋጅ ደንብና መመሪያን በአግባቡ ከመተግበር አንፃር ምን እንደምንመስል ራሳችንን ለመመልከት ይረዳን ዘንድ ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጅቷል።

አክለውም አቶ ጎሳዬ ይህ መድረክ ሁላችንም ብልሹ አሠራርን እንድንጠየፍና የሠራተኞች አዳዲስ የወጡ አዋጆች: ደንቦችና መመሪያዎች ያለንን ግንዛቤ በማሳድግና ግልፀኝነት በመፍጠር ድርሻው የጎላ እንደሚሆን እምነቴ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በተቋሙ ሊከሠቱ የሚችሉ ብልሹና ተገቢ ያልሆኑ አሠራሮችን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለማቀጨጭ አስፈላጊው ጥረት ሁሉ ይደረጋል ሲሉ አስገንዝበዋል ።

በመድረኩ ከፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በአዳዲስ አዋጆች ላይ እንዲሁም ሙስናና ብልሹ አሠራርን አስመልከቶ ደግሞ ከፀረ- ሙስና ኮሚሽን በተጋበዙ አሠልጣኞች የሥልጠና ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ከተሣታፊዎችም ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ከመድረክ ምላሽ ተሠጥባቸዋል።

 

በመጨረሻም ከመድረኩ በቀጣይ ለሚኖሩን ተግባራት በአመራሩና  ባለሙያዎች መካከል ጠንካራ ቲም እስፕሪት በመፍጠርና ግልፀኝነት በማጎልበት በዕቅድ በመመራት ውጤታማ ሥራ ለመሥራት  ከስምምነት በመድረስ መድረኩ ተጠናቋል ።

ጠንካራ የአመራር ሥርዓትና የባለሙያዎች ትጋት የተቋምን ገፅታ ይቀይራል!!

ጥቅምት 2018 ዓ.ም

ሀዋሳ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.