newz31

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የመንገድ ልማት ሥራዎች ያለበትን ደረጃ ገመገሙ።

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የመንገድ ልማት ሥራዎች ያለበትን ደረጃ ገመገሙ::

ግምገማ የተደረገው የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ በበጀት ዓመቱ በመንገዶች ባለስልጣን በኩል እና በገጠር ተደራሽ መንገድ በዩራፕ ዘርፍ ታቅዶ እየተገነቡ ያሉትንና የጥገና መንገዶች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ሥራዎች የግምገማዉ የትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ እየተገመገመ ይገኛል::

በመድረኩም የርዕሰ መስተዳድር አማካሪዎች የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የአራቱም ዞን የፊት አመራሮች እንዲሁም የወረዳ አስተዳዳሪዎችና የፅ/ቤት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል::

በግምገማዉም መድረክ ላይ በመንገዶች ባለስልጣንና በዩራፕ ዘርፍ የታቀዱና በ6 ወር ዉስጥ እስከ አሁን ያለው አፈፃፀምን በተመለከተ የተዘጋጀ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል::

በቀረበው የሪፖርት ሠነድ መነሻ የመድረኩ ተሳታፊዎች ከእቅድ አፈፃፀም አንፃር ያለውን ሁኔታ ከዞን እና ወረዳዎች ደረጃ እታች ያለውን ጉድለትና ጥንካሬ አንስቷው በቀጣይ ልስተካከሉ የሚገባቸውን ዝርዝር ጉዳዮችን በአራት ቡድን ተከፍሎ ጥልቀት ያለው ውይይት እየተደረገ ነው::

የመድረኩ ተሳታፊዎችም በቀጣይ ትኩረት የሚደረጉ በተለይ የዝናብ ወቅት ሳይገባ ቶሎ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅና ከመንገዶች ጥራት አንፃር በቢሮ ደረጃ ትኩረት ልሰጡ የሚገቡ ጉዳዮች ተለይቶ ውይይት በማደረግ ልፈቱ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የውይይት አቅጣጫ ተደርጓል::

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የተጀማመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆኑ አንስተዉ በቀጣይ ከጊዜ ጋር ተያይዞ የምታዩ ችግሮች መፈታት የሚገባቸውና ከመንገዶች ጥራትና እስታንዳርድ ረገድ የሚታዩ ጉድለቶች በተለያ ከግብአት አቅርቦት ጋር ተያይዞ የተስተዋሉት በፍጥነት መታረም ያለባቸው እንደሆነ አቅጣጫ ተቀምጦ ለመንገዶች ግንባታ ስራዎች ሁሉም አካላት መቀናጀት እንዳለባቸዉ ገልፆዎ የቡድን ውይይቱ በጥልቀት በዞን ማዕከል አመራር እየተመራ እየተደረገ ይገኛል::

ከቡድን ውይይት በመቀጠል በጋራ ቡድን ሪፖርት ቀርቦ ማጠቃለያ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል::

ጥር 9 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz82

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልል ደረጃ እየተገነቡ የሚገኙ የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልል ደረጃ እየተገነቡ የሚገኙ የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ::

ርዕሰ መስተዳድሩ ጉብኝት ያደረጉት በክልሉ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ፣ በመንገዶች ባለስልጣን እና በቢሮው ዩራፕ ዘርፍ የተሰሩ የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶችን ነው::

በጉብኝቱም የትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና ምክትል ፕሬዘደንት ክቡር አቶ በየነ ባራሳ፣ የካቢኔ አባላት፣ የዞን አመራሮች፣ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት ተገኝተው እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል::

በበጀት ዓመቱ በዩራፕ ዘርፍ የግንባታ ፕሮጀክቶች 26 የመንገድ ፕሮጀክቶች 153.5 ኪሜ እንዲሁም የጥገና ፕሮጀክቶች 28 መንገድ 198 ኪሜ በክልሉ መንግስት በጀት ተይዞላቸው እየተገነቡ የሚገኙ መንገዶች ተጎብኝቷል::

በበጀት ዓመቱ ሁሉም ፕሮጀክቶች እንዲጠናቀቁ እቅድ ተይዞ እየተሰሩ እንደሆነ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በመስክ ምልከታ ወቅት ገልጸዋል::

በጉብኝቱም ወቅት የመንገድ ስራዎች በሁሉም ዞኖች እና ወረዳዎች ጥራታቸዉ ተጠብቆ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ሁሉም አካላት መረባረብ እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምረው ገልጸዋል::

ጥር 7 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz45

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ::

የመስክ ጉበኝቱ ከቦርጃ ውጅግራ ፕሮጀክት የ5.56 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን የፕሮጀክት ስራዎች ያሉበትን ለማየት ተችሏል:: የመንገዱ ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለማየት ችለናል::

የመንገዱ መገንባት የማልጋ እና የወንዶ ገነት ወረዳን የሚያገናኝ በመሆኑ ለአከባቢው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እጅግ በጣም ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መንገድ እንደሆነ በምልከታ ወቅት ለማረጋገጥ ችለናል:: ለዚህም ፕሮጀክት ሁሉም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የዞን እና ወረዳ አመራሮች በቅርበት ክትትል ማድረግ የሚገባው እንደሆነ ተገልፆዋል::

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአጭር ጊዜ ዉስጥ እስከ ጥር 30/2016 ዓ. ም ድረስ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ የእስታር የሥራ ተቋራጩ አስተባባሪዎች አሳውቋል:: ፕሮጀክቱ በታቀደው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የቢሮ ማናጅመንት አመራሩ በቅርበት ክትትል እንደሚያደርጉ ገልፃዋል::

ጥር 3 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz22

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተደረገ::

በመድረኩ የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ የቢሮ ማናጅመንት አባላት እንዲሁም አጠቃላይ የቢሮ ባለሙያዎች ተገኝተዉ ተሳታፊ ሆኗል:: በግምገማ መድረኩም የ6 ወር የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል::

በቀረበው ሪፖርት መነሻ በ6 ወር ዉስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ዘርፎች እና ዳይረክቶሮቶች በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥሉ እና በአፈፃፀማቸው በመካከለኛ ደረጃ ያሉና ወደ ኃላ የቀሩ ዘርፎች እና ዳይረክቶሬቶች በቀጣይ ቀሪ ወራት በጉድለት የተለዩ ጉዳዮች ትኩረት ተሰጥተው እንዲከናወኑ አቅጣጫ ተቀምጧል::

በመጨረሻም በቢሮ ደረጃ የሚከናወኑ ቁልፍ ቁልፍ ተግባራት በሙሉ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዉስጥ በውጤታማነት እንዲከናወኑ ተግባቦት ላይ ተደርሶ የግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ ተደርጓል::

 ታህሳስ 26 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz2

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የማናጅመንት አባላት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ያሉበትን ደረጃ ጉበኝት አደረጉ ::

በዛሬም የመስክ ጉበኝት የቢሮ አመራሩ ከቦርጃ ውጅግራ ፕሮጀክት የ5.56 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን የፕሮጀክት ስራዎች ያለበትን ለማየት ተችሏል:: በጉብኝቱም የመንገዱ ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ እንደሆነ ለማየት ችለናል::

የመንገዱ መገንባት የማልጋ እና የወንዶ ገነት ወረዳን የሚያገናኝ በመሆኑ ለአከባቢው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እጅግ በጣም ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መንገድ እንደሆነ በምልከታ ወቅት ለማረጋገጥ ችለናል::

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአጭር ጊዜ ዉስጥ እስከ ጥር 30/04/2016 ዓ. ም ድረስ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ የእስታር የሥራ ተቋራጩ አስተባባሪዎች አሳውቋል:: ፕሮጀክቱ በታቀደው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የቢሮ ማናጅመንት አመራሩ በቅርበት ክትትል እንደሚያደርጉ ገልፃዋል::

ታህሣስ 18፣ 2016 ዓ. ም 

ሐዋሳ, ሲዳማ

newss4444

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ በሰሜን ሲዳማ ዞን በለኩ ከተማ አስተዳደር በራማዳ ቀበሌ አቅም ለሌላቸዉ ቤተሰብ የቤት ግንንባታ ማስጀመሪያ ተካሄደ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ በሰሜን ሲዳማ ዞን በለኩ ከተማ አስተዳደር በራማዳ ቀበሌ አቅም ለሌላቸዉ ቤተሰብ የቤት ግንንባታ ማስጀመሪያ ተካሄደ::

በፕሮግራሙም የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች እና ባለሙያዎች የሰሜን ሲዳማ ዞን አመራር እንዲሁም የለኩ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት ለአንዲት አቅመ ደካማ እና 4 ልጆች ላሏት እናት ግንባታ የማስጀመር ስራ ተጀምሯል ::

ይሄ ተግባር የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች እና ባለሙያዎች በራሳቸው ተነሳሽነት እና ፍላጎት ገንዘብ በማዋጣት ያስጀመሩት እንደሆነ ተገልጿል::

በመቀጠልም በለኩ ከተማ አስተዳደር የመናሃሪያ ግቢ ዉስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መሪሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን በቀጣይ መከታተል እና መንከባከብ ከሁሉም የሚጠበቅ እንደሆነ የቢሮ ኃላፊ ተወካይ አስገንዝቧል::

የሰሜን ሲዳማ ዞን ተወካይ በበኩላቸዉ የሲዳማ ህዝብ ያለው ለሌለዉ የማካፈል የባህል እሴት ያለው መሆኑን ጠቅሶ ይሄን ተግባር በቢሮ ደረጃ ማከናወን በመቻሉ በዞኑ ስም ምስጋናቸዉን አቅርቧል::

በሌላም በኩል የለኩ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ፀጋዬ አባቴ መዕልክታቸዉን ሲያስተላልፉ ደሃን እና አቅም የሌላቸዉን መርዳት ፈጣሪ የምደሰትብን ተግባር በመሆኑ በቀጣይ መሰል ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል::

በመቀጠልም ከበጎ ተግባር ጎን ለጎን በለኩ ከተማ አስተዳደር ስለ ትራፊክ አደጋ አስከፊነት ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመንገድ ደህንነት እና መድህን ፈንድ አገልግሎት ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ጋር በመሆን ግ ንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተሰርቷል::

ሐዋሳ, ሲዳማ
መስከረም 10፣ 2016 ዓ.ም.

 

slide19

የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከያ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የቁጥጥር ሥራ በሲዳማ ክልል በይፋ መጀመሩ ተገለጸ፡፡

የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከያ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የቁጥጥር ሥራ በሲዳማ ክልል በይፋ መጀመሩ ተገለጸ፡፡

news84

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ከከልሉ ፖሊስ ኮሚሸንና ከፌዴራል ፖሊስ እንዲሁም ከፌዴራል የትራንስፖርትና ሎጂስትክስ ሚኒስቴር ከመደህን ፈንድ እና መንገድ ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባባር የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላኪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የቁጥጥር ሥራ በይፋ ተጀምሯል፡፡

ድንገተኛ የቁጥጥር ተግባሩ ለተከታታይ 25 ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል፡፡

መስከረም 4/2016 ዓ.ም ሃዋሳ፣ ሲዳማ

news 55

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመልካም አስተዳደርና የካይዘን አተገባበርን በተመለከተ ለቢሮ ሠራተኞች ስልጠና ለመስጠት እና የ2016 ዓ.ም እቅድ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ ተግባቦት ለመፍጠር የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተካሄደ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመልካም አስተዳደርና የካይዘን አተገባበርን በተመለከተ ለቢሮ ሠራተኞች ስልጠና ለመስጠት እና የ2016 ዓ.ም እቅድ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ ተግባቦት ለመፍጠር የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተካሄደ::

በስልጠና እና በውይይት መድረክ ላይ የማናጅመንት አባላት እና አጠቃላይ የቢሮ ሰራተኞች በተገኙበት እየተካሄደ ያለ ሲሆን የተዘጋጀዉ ሰነድ በመልካም አስተዳደር የማስፈን ጉዳዮች እና በካይዘን ስራዎች አተገባበር ዙሪያ ከክልሉ ፓብልክ ሰርቪስ እና የሰው ኃይል ልማት ቢሮ የመጡ ከፍተኛ ባለ እየሰጡ ይገኛሉ::
 
በመቀጠልም የቢሮ የ2016 በጀት ዓመት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርቦ በቢሮ ሰራተኞች ጋር ተግባቦት ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል::
…………………………………..
 
ጳጉሜ,3/2015 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ