bhead

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

bhead

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ ተካሂዷል::

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ አስፋው ጎኔሶ እንደገለፁት ይህ ሴክተር ለሲዳማ ሕዝብ የመልማት ቁጥር አንድ አጀንዳ የሆነውን የመንገድ የልማት ሥራን የሚሰራ ተቋም በመሆኑ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው መስራት ያስፈልጋል ብለዋል::

የመንገድ እና የድልድይ ግንባታ ተደራሽነት እንደ ጥሩ የሚታይ ቢሆንም ከጥራት ጋር ተያይዞ ለሚታዩ ችግሮች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንደሚገባ ተገልጿል::

በሌላም በኩል የትራንስፖርት ዘርፍ አከባቢ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የተደገፈ በማድረግ የሕዝቡን እንግልት ማስቀረት እና የትራፊክ ቁጥጥር ሥራዎችን ሪፎርም በማድረግ የሚታዩ ችግሮች ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይገባል በማለት ተናግሯል::

በመክፈቻው ወቅት የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እንደተናገሩት በቢሮ ደረጃ በመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራዎች በበጀት ዓመቱ ዉጤታማ እንደነበረ ተናግረዋል::

በመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍም በተሰራው ሥራ የሞት መጠን የቀነሰ ቢሆንም  በሰው እና ንብረት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ማስቆም እስካልቻልን ድረስ በመቀናጀት መስራት እንደሚገባ ተጠቅሷል::

በክልል ደረጃ በ2016 በጀት ዓመት 107  የሞት አደጋ መከሰቱንና ከፍተኛ የንብረት ውድመት እና የአካል ጉዳት የደረሰ በመሆኑ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በሙሉ  በመቀናጀት የአደጋ መንስኤን በመለየት መስራትና መከላከል እንደሚገባ ተገልጿል::

በሴክተር ጉባኤው ለዉይይት መነሻ የሆኑ ሰነዶች የ2016 በጀት ዓመት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድን የቢሮው የልማት እቅድ በጀት ክትትል ዳይረክቶሬት ዳይረክተር አቶ ወገኔ ታምራት ያቀረቡ ሲሆን የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከያ የንቅናቄ ሠነድን ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍ ኃላፊ አቅርበው ውይይት ተደርጓል::

rd

የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከል እና አደጋዉን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ ተቋማት እና አካላት በመቀናጀት ከሰሩ የንቅናቄ ሠነዱን ሲያቀርቡ ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ ተናግረዋል::

በመድረኩም የተሻሻለው የትራፊክ ቅጣት ደንብ እና በአደጋ ወቅት የመጀመሪያ ሕክምና ክፍያ ማሻሽያ የተደረገውን ደንብ እስከታች በመውሰድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ በቀረበው ሠነድ ተብራርቷል::

በመጨረሻም በቀረቡት ሰነዶች ላይ ከተሳታፊ አካላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥተው በቀጣይ በሴከተር ደረጃ በቅንጅት በመስራት የተጣሉ ግቦችን ማሳካት አስፈላግ መሆኑን ገልፆዎ ከዞኖች እና ከሐዋሳ ከተማ አስተዳር ጋር በቀጣይ በምሰሩ አቅጣጫዎች ላይ የግቢ ስምምነት ተደርጎ የሴክተር ጉባኤ መድረክ ማጠቃለያ ተደርጓል::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አስፋው ጎኔሶ፣የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ፣ የፕሬዘደንቱ የመሰረተ ልማት አማካሪ ክቡር ዘገዬ ሀሜሶ፣ ክብርት ምንትዋብ ገ/መስቀል የከተማ እና መሰረተ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የዞንና የሐዋሳ ከተማ አመራሮች፣የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የባለድርሻ አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

   =======================

መስከረም, 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

rod

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

rod

ይህ የተገለፀዉ ለአሽከርካሪዎች በሥነ- ምግባር፣ አዲስ በተሻሻሉ የመንገድ ደህንነት ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የመድህን ፈንድ አዋጆችን ለማሳወቅ በተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው።

በመድረኩ በርካታ አሽከርካሪዎች፣ የትራፊክ ፖሊስ አባላት፣ የክልልና መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች  ተሣታፊ ሆነዋል።

road safety 2
road safety 3

የቢሮ ሀላፊ ተወካይና የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ሀላፊ ኮ/ ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የዛሬው መድረክ ዓላማ አሽከርካሪዎች የተከበረ ሙያ ያላችሁ የተከበረውን የሰው ልጅን ህይወት ይዛችሁ የምትንቀሳቀሱ፣ በስነምግባር የታነፃችሁና አዳዲስ ከወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር እንድትተዋወቁ ታሳቢ በማድረግ ነው።

 አክለዉም ባለፈው ዓመት በተከሰተው የትራፊክ አደጋ ዋናው መንስዔ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን ገልፀው በዝግታና በእርጋታ እንድታሽከረክሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሰነዶች ቀርበው በሳል ሙያዊ ገለፃ ተደርጎባቸዋል።

road safety

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አዳነ አየለና የክልሉ መንገድ ደህ/አቅ/ግን/ድህ /አደ/መድህን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ዶካ ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተውባቸው መግባባት ላይ ተደርሶ  መድረኩ ተጠናቋል።

 “በትራፊክ አደጋ አንድም ህይወት እንዳይጠፋ፣ አካል እንዳይጎድል፣ ንብረት እንዳይወድም ሁላችንም ሀላፊነት አለብን! “

 መስከረም 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

nez1

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላክያ የአብይ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላክያ የአብይ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር በየነ ባራሳ, የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ የኮሚቴ አባላት የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

በመድረኩም አጠቃላይ ክልላዊ የትራፊክ አደጋ መከላክያ የመነሻ ሠነድ በቢሮ ኃላፊ በአቶ ታምሩ ታፌ ቀርቦ የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት በማድረግ በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል እንደሆነ በማንሳት ሁሉም እንደ ተቋማቸው ወስደው የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚሰሩ ገልፀዋል::

በተጨማሪም በክልል ደረጃ እንዲሁም በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በወረዳዎች የግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስቷል::

የትራፊክ አደጋ እንዴ ሀገር እያደረሰ ያለዉን ዘርፈ ብዙ ጉዳትን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ እንዲሰሩ ለማድረግ ታቅዶ የተዘጋጀ መድረክ ሲሆን በአስከፍው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት የሞት የአካል ጉዳት እንዲሁም በእኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ እያደረሰ ያለውን ቀውስን ለመቀነስ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ተገልፆዋል::

በመጨረሻም ክቡር ምክትል ፕረዝደንት እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ በቀጣይ ከኮሚቴ ምስረ ታ ጀምሮ በክልል ደረጃ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በቅርበት በቅንጅት በመሥራት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ የድርሻቸውን እንዲወጡ እና ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል::

ሰኔ 03/2016 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ

newz199

ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ሰራተኞች የመጀመሪያውን ክልላዊ የሴክተር መ/ቤቶች ዉድድር አሸናፊ መሆናቸውን ምክንያት በማድረግ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ ::

ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ሰራተኞች የመጀመሪያውን ክልላዊ የሴክተር መ/ቤቶች ዉድድር አሸናፊ መሆናቸውን ምክንያት በማድረግ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ ::

ኮከቦቹ በሀዋሳ ሰማይ ላይ ደመቁ::

የተቋማችንን ተልዕኮ ለማሳለጥና የላቀ ዉጤት ለማስመዝገብ በጋራ ለጋራ ስኬት የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በአጠረ ጊዜ ዉስጥ በመገንባት በመንግሥት ተቋማት የእግር ኳስ የስፖርት ዉድድር ላይ ገና ከጅማሬዉ በሁለቱም ፆታ ያስመዘገብነዉ  ቻምፒዮንነት/ አሸናፊነት የዉስጥ የሴክተራችንን ጠንካራና ደካማ ጎኖቻችንን ለይተን ጥንካሬያችንን ይበልጥ አጎልብተን ጉድለታችንን በፍጥነት አርመንና አካክሰን ለመሥፈንጠር ለጀመርነዉ ጉዞ የትክክለኛ እርምጃ  ማሳያ ዉጤት መሆኑን የተረዳንበት ሕያዉ ምስክር ነዉ።

በመሆኑም ይኸንን ድል በቀጣይ ሁሉም ዘርፎቻችን:ዳይሬክቶሬቶቻችን: ባለሙያዎቻችንና መላዉ መዋቅራችን በተሰጠን ቦታ ከተባበርን ከተደጋገፍን ከተቀናጀን ግልፀኝነትን ፈጥረን ሌብነትና ብልሹ አሠራር በተግባር ተፀይፈን ሕባችንን በፍትሃዊነትና በቅንነት በተሰጠን ጊዜ አገልግለን ዕርካታዉን ካረጋገጥን ሥራችንን በግልፅ መዝኖ የሚገባንን ዉጤት በሚሰጠንና በሚከፍለን እግ/ር: መንግሥት:ፓርቲና ሕዝባችን ፊት ገንዘብ ሊገዛዉ በማይችል ዋጋ የሚተመነዉን ምስክርነትና ሽልማት በአደባባይ ከመቀበል የሚበልጥ ክብርና ዕርካታ ምን አለ? የሴክተራችን ዕንቁና ተወዳጅ የሆናችሁ የማከብራችሁ ባልደረቦቼና  ቤተሰቦቼ ።

ስለዚህ ይህንን አዉቀን በቀሪ ጊዜያችን የአምላካችን የእግ/ር  ዕገዛና ብርታት ፀጋዉን ከሁሉም በላይ አብሮነቱ ጥበቃዉ በዝቶልን ከሚሰጠን ሰላምና አንድነት የሚመነጭ ፍቅር እና ርህራሄ ተላብሰን በዓላማ አንድነት ተጋምደን የሚጠበቅብንን የላቀ ዉጤት አስመዝግበን ለበለጠ ሽልማት እንድንነሳ አደራ እያልኩ ዉድና ዕንቁ የሆናችሁ ተጫዋቾቻችንና የሴክተራችን ሠራተኞች እንዲሁም መላዉ የስፖርቱ ቤተሰቦች ለድካማችሁ ድሉ ስለሚገባችሁ ኮርተንባችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን እላለሁ።

በመጨረሻም ፍፃሜያችን በድል ዋንጫ ታጅቦ በሀዋሳ ሰማይ ላይ ደስታችሁ እንደደመቀ በተሰማራችሁበት ሁሉ ጅማሬያችሁ ሂደታችሁና ፍፃሜያችሁ በአንድነት ለጋራ ድል በጠንካራ ቲሞ ስፕሪት በደስታ በስኬት በፍቅር በዉጤት በድርብ ድል የደመቀ ይሁንላችሁ ።

ብሩህ ጊዜ!

መጋቢት 22/2016 ዓ.ም.

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz112

የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥርና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ከመጋቢት 09 እስከ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገለፀ::

የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥርና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ከመጋቢት 09 እስከ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገለፀ::

በመንገድ የትራፊከ አደጋ ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለመቀነስ የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥርና ግንዛቤ ስራ በሲዳማ ክልል ከመጋቢት 09 -መጋቢት እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ታምሩ ታፌ ለሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ታምሩ ታፌ እንደተናገሩት በህጉ ዙሪያ ለተቆጣጣሪ አካላት እና ለአሽከርካሪዎች ግንዛቤ በመፍጠር በማስተባበር፣በመደገፍ፣ በመከታተልና በመገምገም ህግ የማስከበር ስራው ተጠያቂነት ባለው መልኩ እንዲከናወን ለማድረግ፤በሞተር ሳይክል አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የቁጥጥር ስራ ማከናወን ፣ከክልል የዞንና ወረዳ ኃላፊዎች፣ ትራንስፖርት ተቆጣጣሪ፣ከትራፊክ ፖሊስ አባላት ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር እና በዋናነት ይህን አስከፊ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መቀነስ እንደሆነ በመግለጫቸው ገልፀዋል፡፡

የተቀናጀው የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥርና ግንዛቤ ስራ በመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት አስተባባሪነት በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፤ ከሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ ዋና መምሪያ ጋር በቅንጅት የሚሰራ ይሆናል፡፡

በፕሮግራሙም መሰረት ለአሽከርካሪዎች እና ለተማሪ ትራፊክ ክበብ ኮሚቴዎች የሚሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሐዋሳ ከተማ, በይርጋአለም ከተማ እንዲሁም በአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር እንደሚሰጥ በመግለጫ ወቅት ተገልፆዋል::

የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥርና ግንዛቤ ስራ በሲዳማ ክልል ከሐዋሳ ከተማ አስተዳደር እስከ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በንሳ ዳዬ ድረስ በተመረጡ መስመሮች ላይ የሚከናወን ይሆናል፡፡

መጋቢት 08/2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

newz49

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጥና የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጥና የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

ከክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ፤ከክልሉ ጠቅላይ  ፖሊስ መምሪያ እንዲሁም በየደረጃው ካሉ መዋቅር ጋር በመቀናጀት በክልላችን በተመረጡ ቦታዎች በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በአሮጌው መናኸሪያ ውስጥ :- የሶስተኛ ወገን፣ የቴክኒክ ብቃት ማረጋገጫ ቦሎ፣ የስምሪት ሂደት ፣የተሳፋሪ የትኬት አቆራረጥና መውጫ አሰጣጥን አስመልከቶ እንዲሁም በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መናኸሪያ ዉስጥ ቁጥጥር ተደርጓል:: የቁጥጥርና የተቀናጀ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን በቁጥጥር ወቅት ጎልተው የታዩ ደንብ ተላላፊዎች በህጉና በደንቡ መሠረት ተገቢው እርምጃ ተወስዶባቸዋል ፡፡ 

የተቀናጀውን የቁጥጥር ቡድን በየደረጃው ሥራውን  ያለበት ሂደትና ያጋጠሙ ችግሮችን ከሁለቱም መዋቅር ጋር በመሆን ጎን ለጎን በመገምገም በቦታው እየተፈታ መሄድ እንዳለበትና  የቁጥጥር ተግባሩ አጠናክሮ በማስቀጠል የህግ ማስከበርና የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ስምምነት ላይ ተደርሷል ።

የተቀናጀው የቁጥጥር ቡድን በቀጣይም በሌሎችም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚቀጥል ይሆናል ።

የካቲት 11 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

bheadz2

የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የቢሮው ስፖርት ቡድን የፋይናንስ አቻውን በማሸነፋቸው የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ ::

የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የቢሮው ስፖርት ቡድን የፋይናንስ አቻውን በማሸነፋቸው የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ ::

የቢሮአችን ዕንቁዎች ዋጋችዉ በምንም የማይተመን ብርቅዬዎች ናችሁና ገና ከመነሻዉ በስፖርቱ ያስመዘገባችሁትን ድል በቀጣይም እስከፍፃሜዉ አስጠብቃችሁ ብቻ ሳይሆን የበለጠ እያስመዘገባችሁ እንደምትቀጥሉ እምነቴ ፅኑ ነዉ።

በስፖርቱ የተጀመረው ስኬታማነት በመንገድ ልማት፣ በትራንፖርት ዘርፍ፣ በመንገድ ደህንነትና በሰዉ ተኮር/ በጎ አገልግሎት ሥራዎቻችን ላይ የቢሮአችንን ተልዕኮ ማሳካት ብቻ ሳይሆን የልህቀት ማዕከል አድርገን ማየት ብለን ያስቀመጥነዉን ግብ ተባብረንና ተደጋግፈን የቡድን መንፈስ/team spirit/ ገንብተን ሕዝባችንን ዝቅ ብለን በማገልገል የተገልጋዮቻችንን ዕርካታ በማረጋገጥ ራዕያችንን ዕዉን እንደምናደርግ ለገባነዉ ቃል ኪዳን የማሳኪያ ማሳያ ዉጤት ስለሆነ እንኳን ደስ አለን።

የቀድሞ ቢሮዬ ባልደረቦቼ ሽንፈት መዉደቂያ ሳይሆን ለቀጣይ ስኬት ጉድለትን በመለየት የመፍትሄ አማራጭ በመፈተሽ የድል መንደርደርያ መንገድ ነዉና አይዟችሁ።

 ድልና ድምቀት ለጋራ ራዕያችን ለሁላችን ይሁን ።

newz94

የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ እና የመንገድ ደህንነት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የንቅናቄ መድረክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማጠቃለያ ተደረገ::

የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ እና የመንገድ ደህንነት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የንቅናቄ መድረክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማጠቃለያ ተደረገ::

በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ኃላፊ፣ ክቡር አቶ ዘገዬ ሀመሶ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ፣ የዞን ዋና አስተዳደሪዎ እና የፊት አመራሮች፣ የከተማ አስተዳደር እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት ተደርጓል::

በሴክተር ጉባኤው ላይ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከል ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሠነድ እንዲሁም የባለ ሁለት ጎማ ሞተር አደረጃጀት መመሪያ የጉባኤ አጀንዳዎች ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የጉባኤው ተሳታፊዎችም በቢሮ ደረጃ እስከ ታች እየተከናውኑ ያሉትን ተጨባጭ ለዉጥ እያስመዘገቡ የሚገኙ እንደሆነ አንስተው በተለይ ከመንገድ ልማት ሥራዎች አንፃር ከጥራት ጋር ተያይዞና በጊዜ ከማጠናቀቅ አንፃር ትኩረት ይበልጥ እንዲደረግ ተነስቷል::

በሌላም በኩል በመንገድ የትራፊክ አደጋ መከላከል ረገድ እየመጡ ያሉትን ለዉጦችን በማጠናከር የትራፊክ አደጋ እያስከተለ የሚገኘውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በጋራ በመቀናጀ መቀነስ እንደሚገባ ተገልፆዋል::

በመድረኩም የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ በተነሱ ሃሳቦች ላይ ምላሽ በመስጠት በ ጋራ በመቀናጅት መሥራት ከቻልን በመጨረሻም የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ገልፆዎ በእለቱም ለሴክተር ጉባኤ መሳካት የራሳቸውን ሚና ለተወጡ አካላት የምስጋና እዉቅና ሰርትፊኬት ተሰጥተዉ የእለቱ መድረክ ማጠቃለያ ተደርጓል::

ጥር 17/2016 ዓ.ም