newz11002

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ የሆነው ፊቼ ጫምባላላ የሰላም፣ የእርቅና  እና የአንድነት እሴቶች ጎልቶ የሚታይበት፣ የሲዳማ አባቶች ባማረና ባሸበረቀ የባህልና ስርዓት የሚያከናውኑት  እንዲሁም እንደ ሀገር  ብሩህ ተስፋ የሚሰነቅበት የዘመን መለወጫ በዓል መሆኑ በፕሮግራሙ ተገኝተው በጋራ በተከበረበት ወቅት ተናግሯል።

የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በUNESCO ከማይዳሰሱ ቅርሶች አንዱ በመሆን ከተመዘገበ ዘንድሮ አስረኛ አመቱን ያስቆጠረ ሲሆን በዉስጡ የያዘውን የባህል እሴቶቹን ይበልጥ ማሳደግ እና መንከባከብ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል ::

በዓሉን ስናከብር በአቅም የደከሙትንና በኢኮኖሚ ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ ዜጎችን መርዳት የፍቼ ጫምባላል እሴት በመሆኑ ሁልጊዜ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቅሷል::

የፍቼ ጫምባላላ በዓል የባህል መገለጫ የሆኑት ጉዳዮች በተቋም ዉስጥ ጎልቶ መታየት የሚገባቸው አንድነት፣ ፍቅርና የሰላም  እሴቶች ይበልጥ በሴክተር ዉስጥ በቀጣይም ተጠናክሮ መጎልበት እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ መንከባከብ ሁሉም አመራር እና ሰራተኞች እንደሚጠቅባቸው በመልዕክታቸው ወቅት አበራርተዋል።

የመንገዶች ባለስጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ማቲዎስ በየነ በበኩላቸዉ የፍቼ ጫንባላላ በዓል ከጥንት ጀምሮ በአባቶቻችን ዘንድ ከነበረው እዉቀት ተደምሮ ከሲዳማ አልፎ የዓለም ቅርስ ወደ መሆን የደረሰ በዓል በመሆኑ በሴክተር ዉስጥ የሚገኙ ሰራተኞች እና አመራሩ በጋራ እሴቱን እና ባህሉን ይበልጥ እያማረ እንዲቀጥል መስራት ያስፈልጋል ብለዋል::

በመጨረሻም በዓሉን በማስመልከት በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይረክቶሬት በኩል የተዘጋጁ የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የምግብ ማጉረስና ሌሎች አዝናኝ ፕሮግራሞች ከሀልቾ የኪነት ቡድን ጋር በመሆን በደማቅ ሁኔታ ፕሮግራሙ ተከናውኗል::

መጋቢት 19/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፣ ሲዳማ

p

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::

p

በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ የጉብኝት ቡድን በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን መነሻውን በማድረግ በወረዳዎች እየተሰሩ የሚገኙ የመንገድ ግንባታዎችን እና በሕብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎችን ምልከታ አድርገዋል ::

በምልከታቸውም በፌዴራል የመንገዶች አስተዳደር በኩል ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘውን የአስፓልት መንገድ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎብኝተዋል::

የመንገዱ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ዉስጥ ከማከናወን አንፃር ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮች ተቀርፈው በጥሩ ሁኔታ ግንባታው መከናወን መጀመሩ እጅግ አበራታች እንደሆነ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገልጸዋል::

በሌላም በኩል በክልሉ መንግስት በመንገዶች ባለስልጣን እና በዩራፕ ዘርፍ በኩል ግንባታቸው እየተከናወኑ የሚገኙ መንገዶችን የጥገናና ግንባታ ሂደቶች ያሉበት ሁኔታ ምልከታ ተደርጓል::

በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ግንባታው እየተከናወ የሚገኘው የቦካሶ ዳዋሌ የ16 ኪሜ የመንገድ ግንባታ ሥራ ፕሮጀክት ያለበት ደረጃ መመልከት ተችሏል::

የመንገዱ ግንባታ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ በማድረግ ለአከባቢው ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ብዙ አስተዋፆ ያለው በመሆኑ በመንግስት በኩል ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተብራርቷል::

በተጨማሪም በሕብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉት የመንገድ ከፈታ ሥራዎች የተጎበኙ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች ላይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል ::

በክልሉ በመንግስት በጀት ብቻ የመንገድ ግንባታን በማከናውን ሁሉንም ማህበረሰብ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ተደራሽ  ማድረግ ስለማይቻል በሁሉም ዞኖች አመራሩ ትኩረት በመስጠት ሕዝቡን በማስተባበር የመንገድ ከፈታ እና የገጠር ኮሪደር ሥራዎችን መስራት እንደሚገባቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምሮ ገልጸዋል ::

የቢሮው ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በበኩላቸው በክልል ደረጃ በቢሮ በኩል እየተሰሩ ያሉት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እና ጥራት እንዲጠናቀቁ ከሁሉም የባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ህዝባችን ተጠቃሚ እንዲሆን እንሰራለን በማለት ተናግረዋል::

በጉብኝቱም የሲዳማ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አብርሃም ማርሻሎ የክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የዞን አመራሮች ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል ::

በቀጣይ በሌሎች ዞኖች የጉብኝት ፕሮግራሙ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል::

newz 10013

በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።

በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።

የቢሯችን አመራርና ሠራተኞች በጋራ በመሆን በዓለም ለ37 ጊዜና በሀገራችን ለ36ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኤችአይቪ/ኤድስን ቀን ” ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤችአይቪ/ኤድስ አገልግሎት ለሁሉም ” በሚል መሪ ቃልና እንዲሁም በዓለም ለ33ኛ ጊዜ ና በሀገራችን ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የነጭ ሪቫን ቀንን “የሴት ልጅ ጥቃት የኔም ነው ስለዚህ ዝም አልልም” በሚል መሪ ቃል በጥምረት አክብረዋል።

መድረኩን የከፈቱት የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኮረኔል ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው:- የዛሬው ቀንን ስናከብር ኤችአይቪ/ኤድስና በሴቶችና ህፃናት  ፆታዊ ጥቃት የሀገራችንና የዓለም ችግር ሆኖ እንደቀጠለ ነው። ስለሆነም ሁላችንም ቆም ብለን እራችንን በመመልከት የመከላከል ሀላፊነትና ግዴታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

 በክልሉ ጤና ቢሮ የኤችአይቪ/ኤድስ ሜንስቲሚንግ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት አሸናፊና በክልሉ ሴቶችና ህፃናት ቢሮ የሥርዓተ – ፆታ ሜኒስቲሪሚንግ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት በቀለ አሁናዊ ሆኑ መረጃዎችን የሚያሳዩ ሰነዶችን አቅርበዋል።

በቀረቡት ሠነዶች ላይ አቅራቢዎቹ ያላቸውን ከፍተኛ ልምድና ብቃት በመጠቀም የበሽታውን ስርጭትና መስፋፋት እንዲሁም እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ትንኮሳ መድረኩን ባሳተፈ ውይይት በሳል ግንዛቤ ማስጨበጥ ችለዋል።

ከፍተኛ ባለሙያዎቹም ለተሳታፊዎች ይህ ችግር በሁላችችንም ቤት ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመገንዘብ የዜግነት ግዴታና ሀላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የኤችአይቪ/ኤድስ በደማቸው የሚገኙ ፈቃደኛ የሆኑ ግለሰብም የበሽታውን አስከፊነት በአካል ተገኝተው እንዴት መከላከል እንደሚቻል ተሞክሮአቸውን አስገንዝበዋል።

ተሳታፊዎች በመድረኩ ደስተኛ እንደሆኑና ወቅታዊ መረጃን በማግኘታቸው በመጠንቀቅ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠው መድረኩ ተጠናቋል።

ታህሳስ 2 ፣ 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፣ ሲዳማ

newz 1010

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ብ/ክ/መንግስት የ2017 ዓ.ም ሀገራዊ የተቀናጀ ድንገተኛ የቁጥጥርና ግንዛቤ ሥራ  ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል  ጠቅላይ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እንዲሁም ከሀዋሳ ከተማ አስተዳዳር ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሆነ ተገልጿል ::

የቁጥጥር  ሥራ በተመረጠው የቁጥጥር ቱላ ክፍለ ከተማ ገመጦ ወንዶ ገነት መታጠፊያ  አከባቢ፤ እንዲሁም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጨኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደርና ዳራ ቀባዶ ወረዳ መጪሾ አከባቢ  መስመር  ከሁለቱም ዞን፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት  ጎልተው የታዩ ደንብ መተላለፊያዎች ላይ ቁጥጥር ተደርጓል ::

በተደረገው የተቀናጀ ቁጥጥር ወቅት የደህንነት ቀበቶ አለማሰር፣ የቴክኒክ ምርመራ ቦሎ አለማደስ፣ 3ኛ ወገን አለመግባት፣ ትርፍ ተሳፋሪ መጫን፣ ያልተፈቀደ እስቲከር መለጠፍ፣ ያለ መንጃ ፍቃድ ማሽከርከር እንዲሁም በተለያዩ ደንብ መተላለፎች ላይ ያተኮረ የቁጥጥር ሥራ ተሰርቷል::

በዕለቱ በተሰራው የቁጥጥር ሥራ  በአጠቃላይ 431 ተሽከርካሪዎች የታዩ   ሲሆን፡  ከነዚህ ውስጥ ደንብ ተላልፈው የተገኙ 56 አሽከርካሪዎች  ላይ  ተገቢው የህግ ማስከበር እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ ታውቋል:: ከደንብ ተላላፊዎች  ብር 57,500 (ሃምሳ ሰባት ሺ  አምስት መቶ  ብር) ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በቁጥጥር ወቅት የተወሰነ ክፍተት ያለባቸው አሽከርካሪዎች 375 የሚሆኑት በቀጣይ እንዲያስተካክሉ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት 850 ለሚሆኑ ተሳፋሪዎችና ለ100 ባለ 2 እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችን ጨምሮ ግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ተሰርቷል:: የተቀናጀው ቡድን የቁጥጥር ሥራ በቀሪ ቀናት በተለዩ ቦታዎች ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

24/03/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፥ ሲዳማ

newz 1001

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም ከመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ የተውጣጣ ግብረ ሀይል የድጋፍና ቁጥጥር ሥምሪት እንደተሰጠው ተመላከተ።

የድጋፍና ቁጥጥር ተልዕኮው የሚተገበረው በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማና በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ሲሆን ለ12 ቀናት እንደሚቆይም ተብራርቷል።

የቢሮ ሀላፊው አቶ ታምሩ ታፌ ሥምሪቱን ለግብረ- ሀይሉ ሲሰጡ በንግግራቸው:- ተልዕኳችሁ በዋናነት በመናኽሪያዎች አካባቢ የሚካሄድ የህግና ደንብ ትግበራ በተጨማሪም በእንቅስቃሴ ወቅት አሽከርካሪዎች ደንብና ህግ ጠብቀው ስለመንቀሳቀሳቸው ትኩረት ሠጥተው እንዲሰሩ  አስገንዝበዋል።

አክለውም ተልዕኳችሁ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ተቋማችን ከጎናችሁ ነው ሲሉ አብሮነታቸውን አረጋግጠዋል።

ለተቀናጀ ቁጥጥር ሥራ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ እና የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስቧል::

የከተማ ታክሲ ታሪፍ ጥናት ተሰርቶ በሀዋሳ እና በክልል ከተሞች ተግባራዊ እንዲደረግ በቢሮ በኩል የወረዳውን ተግባራዊነቱ በግብረ ኃይሉ በኩል በትኩረት ጠንካራ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ አስገንዝቧል::

18/03/2017 ዓ.ም.

ሐዋሳ ሲዳማ

newz001

በመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ለመንግስት ሰራተኞች “የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

በመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ለመንግስት ሰራተኞች "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ እንደገለፁት ስልጠናው በሀገር ደረጃ የሚሰጥ እንደመሆኑ ሰራተኞች ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በሀገር ደረጃ እየተሰሩ ያሉትን ሥራዎች እና ቀጣይ የሚተገበሩ ጉዳዮችን በአግባቡ መገንዘብ ይገባል ብለዋል ::

የሰለጠነ የሰው ህይልን በመገንባት ቀልጣፋ እና ዉጤታማ ሥራ እንዲሰሩ ለማድረግ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገልጿል::

ለስልጠናው መድረክ የተዘጋጀ ሠነድ በንባብ የቀረበ ሲሆን ስልጠናው ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል ::

ህዳር 2/2017 ዓ.ም. ፣ ሐዋሳ

bhead

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

bhead

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ ተካሂዷል::

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ አስፋው ጎኔሶ እንደገለፁት ይህ ሴክተር ለሲዳማ ሕዝብ የመልማት ቁጥር አንድ አጀንዳ የሆነውን የመንገድ የልማት ሥራን የሚሰራ ተቋም በመሆኑ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው መስራት ያስፈልጋል ብለዋል::

የመንገድ እና የድልድይ ግንባታ ተደራሽነት እንደ ጥሩ የሚታይ ቢሆንም ከጥራት ጋር ተያይዞ ለሚታዩ ችግሮች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንደሚገባ ተገልጿል::

በሌላም በኩል የትራንስፖርት ዘርፍ አከባቢ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የተደገፈ በማድረግ የሕዝቡን እንግልት ማስቀረት እና የትራፊክ ቁጥጥር ሥራዎችን ሪፎርም በማድረግ የሚታዩ ችግሮች ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይገባል በማለት ተናግሯል::

በመክፈቻው ወቅት የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እንደተናገሩት በቢሮ ደረጃ በመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራዎች በበጀት ዓመቱ ዉጤታማ እንደነበረ ተናግረዋል::

በመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍም በተሰራው ሥራ የሞት መጠን የቀነሰ ቢሆንም  በሰው እና ንብረት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ማስቆም እስካልቻልን ድረስ በመቀናጀት መስራት እንደሚገባ ተጠቅሷል::

በክልል ደረጃ በ2016 በጀት ዓመት 107  የሞት አደጋ መከሰቱንና ከፍተኛ የንብረት ውድመት እና የአካል ጉዳት የደረሰ በመሆኑ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በሙሉ  በመቀናጀት የአደጋ መንስኤን በመለየት መስራትና መከላከል እንደሚገባ ተገልጿል::

በሴክተር ጉባኤው ለዉይይት መነሻ የሆኑ ሰነዶች የ2016 በጀት ዓመት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድን የቢሮው የልማት እቅድ በጀት ክትትል ዳይረክቶሬት ዳይረክተር አቶ ወገኔ ታምራት ያቀረቡ ሲሆን የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከያ የንቅናቄ ሠነድን ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍ ኃላፊ አቅርበው ውይይት ተደርጓል::

rd

የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከል እና አደጋዉን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ ተቋማት እና አካላት በመቀናጀት ከሰሩ የንቅናቄ ሠነዱን ሲያቀርቡ ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ ተናግረዋል::

በመድረኩም የተሻሻለው የትራፊክ ቅጣት ደንብ እና በአደጋ ወቅት የመጀመሪያ ሕክምና ክፍያ ማሻሽያ የተደረገውን ደንብ እስከታች በመውሰድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ በቀረበው ሠነድ ተብራርቷል::

በመጨረሻም በቀረቡት ሰነዶች ላይ ከተሳታፊ አካላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥተው በቀጣይ በሴከተር ደረጃ በቅንጅት በመስራት የተጣሉ ግቦችን ማሳካት አስፈላግ መሆኑን ገልፆዎ ከዞኖች እና ከሐዋሳ ከተማ አስተዳር ጋር በቀጣይ በምሰሩ አቅጣጫዎች ላይ የግቢ ስምምነት ተደርጎ የሴክተር ጉባኤ መድረክ ማጠቃለያ ተደርጓል::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አስፋው ጎኔሶ፣የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ፣ የፕሬዘደንቱ የመሰረተ ልማት አማካሪ ክቡር ዘገዬ ሀሜሶ፣ ክብርት ምንትዋብ ገ/መስቀል የከተማ እና መሰረተ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የዞንና የሐዋሳ ከተማ አመራሮች፣የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የባለድርሻ አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

   =======================

መስከረም, 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

rod

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

rod

ይህ የተገለፀዉ ለአሽከርካሪዎች በሥነ- ምግባር፣ አዲስ በተሻሻሉ የመንገድ ደህንነት ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የመድህን ፈንድ አዋጆችን ለማሳወቅ በተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው።

በመድረኩ በርካታ አሽከርካሪዎች፣ የትራፊክ ፖሊስ አባላት፣ የክልልና መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች  ተሣታፊ ሆነዋል።

road safety 2
road safety 3

የቢሮ ሀላፊ ተወካይና የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ሀላፊ ኮ/ ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የዛሬው መድረክ ዓላማ አሽከርካሪዎች የተከበረ ሙያ ያላችሁ የተከበረውን የሰው ልጅን ህይወት ይዛችሁ የምትንቀሳቀሱ፣ በስነምግባር የታነፃችሁና አዳዲስ ከወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር እንድትተዋወቁ ታሳቢ በማድረግ ነው።

 አክለዉም ባለፈው ዓመት በተከሰተው የትራፊክ አደጋ ዋናው መንስዔ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን ገልፀው በዝግታና በእርጋታ እንድታሽከረክሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሰነዶች ቀርበው በሳል ሙያዊ ገለፃ ተደርጎባቸዋል።

road safety

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አዳነ አየለና የክልሉ መንገድ ደህ/አቅ/ግን/ድህ /አደ/መድህን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ዶካ ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተውባቸው መግባባት ላይ ተደርሶ  መድረኩ ተጠናቋል።

 “በትራፊክ አደጋ አንድም ህይወት እንዳይጠፋ፣ አካል እንዳይጎድል፣ ንብረት እንዳይወድም ሁላችንም ሀላፊነት አለብን! “

 መስከረም 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ