11111

የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደረገ::

የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደረገ::

የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ በክልል ደረጃ እየደረሰ ያለዉን የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከባለ ድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሂዷል::

የምክክር እና ስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የመንገድ ደህንነና መድን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ኮሮነል ሮዳሞ ኪአ እንደተናገሩት በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የመንገድ ትራፊክ አደጋ መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ተናግሯል::

በሲዳማ ክልል ባለፉት አራት ዓመታት ከ 2014 እስከ 2017 ድረስ ብቻ 474 ዜጎች በሞትእና 313 ዘጎች ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን እና ከ 30 ሚሊዮን በላይ የሚገመት ንብረት መዉደሙን ገልፆዋል::

በሌላም በኩል በ 2017 በጀት ዓመት ብቻ ወደ 180 ዜጎች በመንገድ ትራፊክ አደጋ የሞት አደጋ የደረሰባቸው እንደሆነ አስረድቷል::

በተጨማሪም በክልል ደረጃ 89.9 % አደጋ እየደረሰ ያለዉ ከተፈቀደው ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከሩ መንስኤ መሆኑን ጠቅሰዉ አስከርካሪዎች ለዚህ ሚናቸው ከፍተኝበመሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል::

የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት በብቃት በማሰልጠን  ኃላፊነታቸዉን በመዎጣት መንግስት ያወጣዉን ደንብ እና አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ እንዲወጡ አሳስቧል::

በክልል ደረጃ ለትራፊክ አደጋ መከሰት መንስኤ ከሆኑት ጉዳዮች ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት, አሽከርካሪዎች  ደንብን አለማሽከርከር ለትራፊክ  አደጋ መከሰት ምክንያት መሆኑን ገልፆዋል::

በሌላም በኩል የተሽከራካሪ ብቃት ማረጋገጫ ተቋማት በቃት ሌላቸው ተሽከርካሪዎች የብቃት ማረጋገጫ መስጠት የሚታዩ ችግሮች መሆኑ ተነስቷል::

በምክክሩ መድረክ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በትራንስፖርት እንቅስቃሴ ወቅት የሚደርሱ የመንገድ ትራፊክ አደጋን የመከላከል ጉዳይ ለመንግስት አካላት ብቻ የሚተዉ ሳይሆን የማሰልጠኛ ተቋማት, የትራንስፖርት ማህበራት የቴክኒክ ምርመራ እንዲሁም ኢንሹራንሶች አደጋዉን ለመቀነስ ሚናችን ትልቅ በመሆኑ ግዴታቸንን እንወጣለን በማለት ገልፆዋል::

በመጨረሻም የመንገድ ደህንነት እና መድን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ኮሮነል ሮዳሞ ኪአ እና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታምሬ ሪቂዋ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል::

በምክክር መድረኩ ላይ የቢሮ ምክትል ኃላፊዎች የክልል ፖሊስ ኮሚሽን, የሐዋሳ ከተማ የመ/ል/ት/መምሪያ ኃላፊዎች የ ትራንስፖርት ማህበራት,የማሰልጠኛ ተቋማት, እንሱራንሶች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት በሙሉ ተገኝተዉ ተሳታፊ ሆነዋል::

ነሐሴ, 2017 ዓ.ም ሐዋሳ

newz100012

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ድጋፍ እና ክትትል ግብረ መልስ ተሰጠ፡፡

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ድጋፍ እና ክትትል ግብረ መልስ ተሰጠ፡፡

በበጀት ዓመቱ በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የመንገድ እና ድልድይ ግንባታ መሰረተ ልማትን ለማፋጠን ትኩረት ተሰጥተዉ እየተሰራ የቆየ ሲሆን በመንግስት በጀት ብቻ በየዓመቱ በጀት ተይዞ የማህበረሰቡን የመንገድ ጥያቄዎችን መመለስ አስቸጋር በመሆኑ ህበረተሰቡን በማሳተፍ የመንገድ እና የድልድይ ግንባታ ሥራዎች በሁሉም ወረዳዎች እንዲከናወኑ ተደርጓል፡፡

በዚህም በዓመቱ ለማከናወን ዕቅድ ከተያዙ አዳዲስ የመንገድ ከፈታ እና የጥገና ስራዎች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ከመንግስት በጀት ዉጪ ህበረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደተቻለ ለዞኖች በዓመቱ የተከናወኑ ሥራዎችን መነሻ በማድረግ ግበረ መልስ በተሰጠበት ወቅት ተገልጿል፡፡

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን ደረጃ ህበረተሰቡን በማሳተፍ በተሰራው ስራ በሁሉም  ወረዳዎች አደረጃጀቶችን እስከ ቀበሌ ድረስ በመጠቀም በሁሉም ቀበሌያት በልማት ቡድን ንቅናቄ ተደርጎ በተሰራዉ ሥራ ማህበረሰቡ ተጠቃሚ መሆን መቻሉን በተሰጠው ግብረ መልስ በተሰጠበት ወቅት ተገልጿል:: 

በዞን ደረጃ ከቢሮ ጋር በመቀናጀት እስከታችኛዉ መዋቅር ድረስ እቅድ በማዉረድ እንዲተገበር ለማድረግ በተቀመጠዉ እስታንዳርድ መሰረት ከ6-8 ሜትር  ድረስ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሶ የከፈታ እና ጥገና ሥራ ማከናወን መቻሉን  ተገልጿል፡፡

የወጣውን የመንገድ እሰታንዳርድ መነሻ ከማከናወን አንጻር በአንዳንድ ወረዳዎች ላይ ጉድለቶች መታየቸውን እና እቅዱን በሁሉም ቀበሌ  ተደራሸ አለማድግ፤ ከእስታንዳርድ በታች የመንገደ ከፈታ ማከናወን እና መንደርን ከመንደር ከማገናኝት ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ እና በቀጣይ በጀት ዓመት ማረም የሚገባቸው እንደሆነ ተብራርቷል፡፡

በግበረ መልሱ መድረክ ላይ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳር  አቶ መንገሻ ፊታሞ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ህብረት ቢያ የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የወረዳ አመራሮች ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል ፡፡

ስኔ 18/2017 ዓ.ም 

ሀዋሳ፣ሲዳማ

newz11002

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ የሆነው ፊቼ ጫምባላላ የሰላም፣ የእርቅና  እና የአንድነት እሴቶች ጎልቶ የሚታይበት፣ የሲዳማ አባቶች ባማረና ባሸበረቀ የባህልና ስርዓት የሚያከናውኑት  እንዲሁም እንደ ሀገር  ብሩህ ተስፋ የሚሰነቅበት የዘመን መለወጫ በዓል መሆኑ በፕሮግራሙ ተገኝተው በጋራ በተከበረበት ወቅት ተናግሯል።

የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በUNESCO ከማይዳሰሱ ቅርሶች አንዱ በመሆን ከተመዘገበ ዘንድሮ አስረኛ አመቱን ያስቆጠረ ሲሆን በዉስጡ የያዘውን የባህል እሴቶቹን ይበልጥ ማሳደግ እና መንከባከብ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል ::

በዓሉን ስናከብር በአቅም የደከሙትንና በኢኮኖሚ ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ ዜጎችን መርዳት የፍቼ ጫምባላል እሴት በመሆኑ ሁልጊዜ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቅሷል::

የፍቼ ጫምባላላ በዓል የባህል መገለጫ የሆኑት ጉዳዮች በተቋም ዉስጥ ጎልቶ መታየት የሚገባቸው አንድነት፣ ፍቅርና የሰላም  እሴቶች ይበልጥ በሴክተር ዉስጥ በቀጣይም ተጠናክሮ መጎልበት እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ መንከባከብ ሁሉም አመራር እና ሰራተኞች እንደሚጠቅባቸው በመልዕክታቸው ወቅት አበራርተዋል።

የመንገዶች ባለስጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ማቲዎስ በየነ በበኩላቸዉ የፍቼ ጫንባላላ በዓል ከጥንት ጀምሮ በአባቶቻችን ዘንድ ከነበረው እዉቀት ተደምሮ ከሲዳማ አልፎ የዓለም ቅርስ ወደ መሆን የደረሰ በዓል በመሆኑ በሴክተር ዉስጥ የሚገኙ ሰራተኞች እና አመራሩ በጋራ እሴቱን እና ባህሉን ይበልጥ እያማረ እንዲቀጥል መስራት ያስፈልጋል ብለዋል::

በመጨረሻም በዓሉን በማስመልከት በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይረክቶሬት በኩል የተዘጋጁ የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የምግብ ማጉረስና ሌሎች አዝናኝ ፕሮግራሞች ከሀልቾ የኪነት ቡድን ጋር በመሆን በደማቅ ሁኔታ ፕሮግራሙ ተከናውኗል::

መጋቢት 19/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፣ ሲዳማ

newz10222

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::

ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::

p

በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ የጉብኝት ቡድን በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን መነሻውን በማድረግ በወረዳዎች እየተሰሩ የሚገኙ የመንገድ ግንባታዎችን እና በሕብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎችን ምልከታ አድርገዋል ::

በምልከታቸውም በፌዴራል የመንገዶች አስተዳደር በኩል ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘውን የአስፓልት መንገድ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎብኝተዋል::

የመንገዱ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ዉስጥ ከማከናወን አንፃር ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮች ተቀርፈው በጥሩ ሁኔታ ግንባታው መከናወን መጀመሩ እጅግ አበራታች እንደሆነ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገልጸዋል::

በሌላም በኩል በክልሉ መንግስት በመንገዶች ባለስልጣን እና በዩራፕ ዘርፍ በኩል ግንባታቸው እየተከናወኑ የሚገኙ መንገዶችን የጥገናና ግንባታ ሂደቶች ያሉበት ሁኔታ ምልከታ ተደርጓል::

በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ግንባታው እየተከናወ የሚገኘው የቦካሶ ዳዋሌ የ16 ኪሜ የመንገድ ግንባታ ሥራ ፕሮጀክት ያለበት ደረጃ መመልከት ተችሏል::

የመንገዱ ግንባታ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ በማድረግ ለአከባቢው ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ብዙ አስተዋፆ ያለው በመሆኑ በመንግስት በኩል ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተብራርቷል::

በተጨማሪም በሕብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉት የመንገድ ከፈታ ሥራዎች የተጎበኙ ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች ላይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል ::

በክልሉ በመንግስት በጀት ብቻ የመንገድ ግንባታን በማከናውን ሁሉንም ማህበረሰብ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ተደራሽ  ማድረግ ስለማይቻል በሁሉም ዞኖች አመራሩ ትኩረት በመስጠት ሕዝቡን በማስተባበር የመንገድ ከፈታ እና የገጠር ኮሪደር ሥራዎችን መስራት እንደሚገባቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ጨምሮ ገልጸዋል ::

የቢሮው ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ በበኩላቸው በክልል ደረጃ በቢሮ በኩል እየተሰሩ ያሉት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እና ጥራት እንዲጠናቀቁ ከሁሉም የባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ህዝባችን ተጠቃሚ እንዲሆን እንሰራለን በማለት ተናግረዋል::

በጉብኝቱም የሲዳማ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አብርሃም ማርሻሎ የክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የዞን አመራሮች ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል ::

በቀጣይ በሌሎች ዞኖች የጉብኝት ፕሮግራሙ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል::

newz 10013

በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።

በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።

የቢሯችን አመራርና ሠራተኞች በጋራ በመሆን በዓለም ለ37 ጊዜና በሀገራችን ለ36ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኤችአይቪ/ኤድስን ቀን ” ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤችአይቪ/ኤድስ አገልግሎት ለሁሉም ” በሚል መሪ ቃልና እንዲሁም በዓለም ለ33ኛ ጊዜ ና በሀገራችን ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የነጭ ሪቫን ቀንን “የሴት ልጅ ጥቃት የኔም ነው ስለዚህ ዝም አልልም” በሚል መሪ ቃል በጥምረት አክብረዋል።

መድረኩን የከፈቱት የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኮረኔል ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው:- የዛሬው ቀንን ስናከብር ኤችአይቪ/ኤድስና በሴቶችና ህፃናት  ፆታዊ ጥቃት የሀገራችንና የዓለም ችግር ሆኖ እንደቀጠለ ነው። ስለሆነም ሁላችንም ቆም ብለን እራችንን በመመልከት የመከላከል ሀላፊነትና ግዴታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

 በክልሉ ጤና ቢሮ የኤችአይቪ/ኤድስ ሜንስቲሚንግ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት አሸናፊና በክልሉ ሴቶችና ህፃናት ቢሮ የሥርዓተ – ፆታ ሜኒስቲሪሚንግ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት በቀለ አሁናዊ ሆኑ መረጃዎችን የሚያሳዩ ሰነዶችን አቅርበዋል።

በቀረቡት ሠነዶች ላይ አቅራቢዎቹ ያላቸውን ከፍተኛ ልምድና ብቃት በመጠቀም የበሽታውን ስርጭትና መስፋፋት እንዲሁም እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ትንኮሳ መድረኩን ባሳተፈ ውይይት በሳል ግንዛቤ ማስጨበጥ ችለዋል።

ከፍተኛ ባለሙያዎቹም ለተሳታፊዎች ይህ ችግር በሁላችችንም ቤት ሊከሰት የሚችል መሆኑን በመገንዘብ የዜግነት ግዴታና ሀላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የኤችአይቪ/ኤድስ በደማቸው የሚገኙ ፈቃደኛ የሆኑ ግለሰብም የበሽታውን አስከፊነት በአካል ተገኝተው እንዴት መከላከል እንደሚቻል ተሞክሮአቸውን አስገንዝበዋል።

ተሳታፊዎች በመድረኩ ደስተኛ እንደሆኑና ወቅታዊ መረጃን በማግኘታቸው በመጠንቀቅ ሀላፊነታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠው መድረኩ ተጠናቋል።

ታህሳስ 2 ፣ 2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፣ ሲዳማ

newz 1010

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ብ/ክ/መንግስት የ2017 ዓ.ም ሀገራዊ የተቀናጀ ድንገተኛ የቁጥጥርና ግንዛቤ ሥራ  ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል  ጠቅላይ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እንዲሁም ከሀዋሳ ከተማ አስተዳዳር ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሆነ ተገልጿል ::

የቁጥጥር  ሥራ በተመረጠው የቁጥጥር ቱላ ክፍለ ከተማ ገመጦ ወንዶ ገነት መታጠፊያ  አከባቢ፤ እንዲሁም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጨኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደርና ዳራ ቀባዶ ወረዳ መጪሾ አከባቢ  መስመር  ከሁለቱም ዞን፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት  ጎልተው የታዩ ደንብ መተላለፊያዎች ላይ ቁጥጥር ተደርጓል ::

በተደረገው የተቀናጀ ቁጥጥር ወቅት የደህንነት ቀበቶ አለማሰር፣ የቴክኒክ ምርመራ ቦሎ አለማደስ፣ 3ኛ ወገን አለመግባት፣ ትርፍ ተሳፋሪ መጫን፣ ያልተፈቀደ እስቲከር መለጠፍ፣ ያለ መንጃ ፍቃድ ማሽከርከር እንዲሁም በተለያዩ ደንብ መተላለፎች ላይ ያተኮረ የቁጥጥር ሥራ ተሰርቷል::

በዕለቱ በተሰራው የቁጥጥር ሥራ  በአጠቃላይ 431 ተሽከርካሪዎች የታዩ   ሲሆን፡  ከነዚህ ውስጥ ደንብ ተላልፈው የተገኙ 56 አሽከርካሪዎች  ላይ  ተገቢው የህግ ማስከበር እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ ታውቋል:: ከደንብ ተላላፊዎች  ብር 57,500 (ሃምሳ ሰባት ሺ  አምስት መቶ  ብር) ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በቁጥጥር ወቅት የተወሰነ ክፍተት ያለባቸው አሽከርካሪዎች 375 የሚሆኑት በቀጣይ እንዲያስተካክሉ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት 850 ለሚሆኑ ተሳፋሪዎችና ለ100 ባለ 2 እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችን ጨምሮ ግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ተሰርቷል:: የተቀናጀው ቡድን የቁጥጥር ሥራ በቀሪ ቀናት በተለዩ ቦታዎች ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

24/03/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፥ ሲዳማ

newz 1001

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም ከመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ የተውጣጣ ግብረ ሀይል የድጋፍና ቁጥጥር ሥምሪት እንደተሰጠው ተመላከተ።

የድጋፍና ቁጥጥር ተልዕኮው የሚተገበረው በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማና በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ሲሆን ለ12 ቀናት እንደሚቆይም ተብራርቷል።

የቢሮ ሀላፊው አቶ ታምሩ ታፌ ሥምሪቱን ለግብረ- ሀይሉ ሲሰጡ በንግግራቸው:- ተልዕኳችሁ በዋናነት በመናኽሪያዎች አካባቢ የሚካሄድ የህግና ደንብ ትግበራ በተጨማሪም በእንቅስቃሴ ወቅት አሽከርካሪዎች ደንብና ህግ ጠብቀው ስለመንቀሳቀሳቸው ትኩረት ሠጥተው እንዲሰሩ  አስገንዝበዋል።

አክለውም ተልዕኳችሁ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ተቋማችን ከጎናችሁ ነው ሲሉ አብሮነታቸውን አረጋግጠዋል።

ለተቀናጀ ቁጥጥር ሥራ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ እና የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስቧል::

የከተማ ታክሲ ታሪፍ ጥናት ተሰርቶ በሀዋሳ እና በክልል ከተሞች ተግባራዊ እንዲደረግ በቢሮ በኩል የወረዳውን ተግባራዊነቱ በግብረ ኃይሉ በኩል በትኩረት ጠንካራ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ አስገንዝቧል::

18/03/2017 ዓ.ም.

ሐዋሳ ሲዳማ

newz001

በመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ለመንግስት ሰራተኞች “የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

በመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ለመንግስት ሰራተኞች "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ እንደገለፁት ስልጠናው በሀገር ደረጃ የሚሰጥ እንደመሆኑ ሰራተኞች ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በሀገር ደረጃ እየተሰሩ ያሉትን ሥራዎች እና ቀጣይ የሚተገበሩ ጉዳዮችን በአግባቡ መገንዘብ ይገባል ብለዋል ::

የሰለጠነ የሰው ህይልን በመገንባት ቀልጣፋ እና ዉጤታማ ሥራ እንዲሰሩ ለማድረግ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገልጿል::

ለስልጠናው መድረክ የተዘጋጀ ሠነድ በንባብ የቀረበ ሲሆን ስልጠናው ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል ::

ህዳር 2/2017 ዓ.ም. ፣ ሐዋሳ