በመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ለመንግስት ሰራተኞች "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ እንደገለፁት ስልጠናው በሀገር ደረጃ የሚሰጥ እንደመሆኑ ሰራተኞች ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም በሀገር ደረጃ እየተሰሩ ያሉትን ሥራዎች እና ቀጣይ የሚተገበሩ ጉዳዮችን በአግባቡ መገንዘብ ይገባል ብለዋል ::


የሰለጠነ የሰው ህይልን በመገንባት ቀልጣፋ እና ዉጤታማ ሥራ እንዲሰሩ ለማድረግ በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገልጿል::


ለስልጠናው መድረክ የተዘጋጀ ሠነድ በንባብ የቀረበ ሲሆን ስልጠናው ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል ::
ህዳር 2/2017 ዓ.ም. ፣ ሐዋሳ
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::