የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላክያ የአብይ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር በየነ ባራሳ, የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ የኮሚቴ አባላት የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::
በመድረኩም አጠቃላይ ክልላዊ የትራፊክ አደጋ መከላክያ የመነሻ ሠነድ በቢሮ ኃላፊ በአቶ ታምሩ ታፌ ቀርቦ የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት በማድረግ በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል እንደሆነ በማንሳት ሁሉም እንደ ተቋማቸው ወስደው የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚሰሩ ገልፀዋል::

በተጨማሪም በክልል ደረጃ እንዲሁም በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በወረዳዎች የግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስቷል::
የትራፊክ አደጋ እንዴ ሀገር እያደረሰ ያለዉን ዘርፈ ብዙ ጉዳትን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ እንዲሰሩ ለማድረግ ታቅዶ የተዘጋጀ መድረክ ሲሆን በአስከፍው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት የሞት የአካል ጉዳት እንዲሁም በእኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ እያደረሰ ያለውን ቀውስን ለመቀነስ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ተገልፆዋል::

በመጨረሻም ክቡር ምክትል ፕረዝደንት እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ በቀጣይ ከኮሚቴ ምስረ ታ ጀምሮ በክልል ደረጃ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በቅርበት በቅንጅት በመሥራት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ የድርሻቸውን እንዲወጡ እና ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል::
ሰኔ 03/2016 ዓ.ም
ሐዋሳ, ሲዳማ
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::