የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ የቢሮው ስፖርት ቡድን የፋይናንስ አቻውን በማሸነፋቸው የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ ::

የቢሮአችን ዕንቁዎች ዋጋችዉ በምንም የማይተመን ብርቅዬዎች ናችሁና ገና ከመነሻዉ በስፖርቱ ያስመዘገባችሁትን ድል በቀጣይም እስከፍፃሜዉ አስጠብቃችሁ ብቻ ሳይሆን የበለጠ እያስመዘገባችሁ እንደምትቀጥሉ እምነቴ ፅኑ ነዉ።
በስፖርቱ የተጀመረው ስኬታማነት በመንገድ ልማት፣ በትራንፖርት ዘርፍ፣ በመንገድ ደህንነትና በሰዉ ተኮር/ በጎ አገልግሎት ሥራዎቻችን ላይ የቢሮአችንን ተልዕኮ ማሳካት ብቻ ሳይሆን የልህቀት ማዕከል አድርገን ማየት ብለን ያስቀመጥነዉን ግብ ተባብረንና ተደጋግፈን የቡድን መንፈስ/team spirit/ ገንብተን ሕዝባችንን ዝቅ ብለን በማገልገል የተገልጋዮቻችንን ዕርካታ በማረጋገጥ ራዕያችንን ዕዉን እንደምናደርግ ለገባነዉ ቃል ኪዳን የማሳኪያ ማሳያ ዉጤት ስለሆነ እንኳን ደስ አለን።

የቀድሞ ቢሮዬ ባልደረቦቼ ሽንፈት መዉደቂያ ሳይሆን ለቀጣይ ስኬት ጉድለትን በመለየት የመፍትሄ አማራጭ በመፈተሽ የድል መንደርደርያ መንገድ ነዉና አይዟችሁ።
ድልና ድምቀት ለጋራ ራዕያችን ለሁላችን ይሁን ።
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በጋራ በተገኙበት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በደመቀ መልኩ ተከበረ::
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሲዳማ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ::
በመዘናጋት ሥርጭቱ እየተዛመተ ያለውን የኤችአይቪ/ኤድስንና በሴቶችና ህፃናት ላይ እየደረሰ ያለውን ፆታዊ ጥቃት በጋራ መከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ።
በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::
በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::