የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የመንገድ ልማት ሥራዎች ያለበትን ደረጃ ገመገሙ።

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የመንገድ ልማት ሥራዎች ያለበትን ደረጃ ገመገሙ::

ግምገማ የተደረገው የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ በበጀት ዓመቱ በመንገዶች ባለስልጣን በኩል እና በገጠር ተደራሽ መንገድ በዩራፕ ዘርፍ ታቅዶ እየተገነቡ ያሉትንና የጥገና መንገዶች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ሥራዎች የግምገማዉ የትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ እየተገመገመ ይገኛል::

በመድረኩም የርዕሰ መስተዳድር አማካሪዎች የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እና የማናጅመንት አባላት የአራቱም ዞን የፊት አመራሮች እንዲሁም የወረዳ አስተዳዳሪዎችና የፅ/ቤት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል::

በግምገማዉም መድረክ ላይ በመንገዶች ባለስልጣንና በዩራፕ ዘርፍ የታቀዱና በ6 ወር ዉስጥ እስከ አሁን ያለው አፈፃፀምን በተመለከተ የተዘጋጀ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል::

በቀረበው የሪፖርት ሠነድ መነሻ የመድረኩ ተሳታፊዎች ከእቅድ አፈፃፀም አንፃር ያለውን ሁኔታ ከዞን እና ወረዳዎች ደረጃ እታች ያለውን ጉድለትና ጥንካሬ አንስቷው በቀጣይ ልስተካከሉ የሚገባቸውን ዝርዝር ጉዳዮችን በአራት ቡድን ተከፍሎ ጥልቀት ያለው ውይይት እየተደረገ ነው::

የመድረኩ ተሳታፊዎችም በቀጣይ ትኩረት የሚደረጉ በተለይ የዝናብ ወቅት ሳይገባ ቶሎ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅና ከመንገዶች ጥራት አንፃር በቢሮ ደረጃ ትኩረት ልሰጡ የሚገቡ ጉዳዮች ተለይቶ ውይይት በማደረግ ልፈቱ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የውይይት አቅጣጫ ተደርጓል::

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ የተጀማመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆኑ አንስተዉ በቀጣይ ከጊዜ ጋር ተያይዞ የምታዩ ችግሮች መፈታት የሚገባቸውና ከመንገዶች ጥራትና እስታንዳርድ ረገድ የሚታዩ ጉድለቶች በተለያ ከግብአት አቅርቦት ጋር ተያይዞ የተስተዋሉት በፍጥነት መታረም ያለባቸው እንደሆነ አቅጣጫ ተቀምጦ ለመንገዶች ግንባታ ስራዎች ሁሉም አካላት መቀናጀት እንዳለባቸዉ ገልፆዎ የቡድን ውይይቱ በጥልቀት በዞን ማዕከል አመራር እየተመራ እየተደረገ ይገኛል::

ከቡድን ውይይት በመቀጠል በጋራ ቡድን ሪፖርት ቀርቦ ማጠቃለያ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል::

ጥር 9 /2016 ዓ.ም

ሐዋሳ, ሲዳማ

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Comments are closed.