newz 1010

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ክልል የተቀናጀ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ተጠናክሮ ቀጥሏል ::

በሲዳማ ብ/ክ/መንግስት የ2017 ዓ.ም ሀገራዊ የተቀናጀ ድንገተኛ የቁጥጥርና ግንዛቤ ሥራ  ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል  ጠቅላይ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እንዲሁም ከሀዋሳ ከተማ አስተዳዳር ጋር በመቀናጀት እየተሰራ እንደሆነ ተገልጿል ::

የቁጥጥር  ሥራ በተመረጠው የቁጥጥር ቱላ ክፍለ ከተማ ገመጦ ወንዶ ገነት መታጠፊያ  አከባቢ፤ እንዲሁም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጨኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደርና ዳራ ቀባዶ ወረዳ መጪሾ አከባቢ  መስመር  ከሁለቱም ዞን፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት  ጎልተው የታዩ ደንብ መተላለፊያዎች ላይ ቁጥጥር ተደርጓል ::

በተደረገው የተቀናጀ ቁጥጥር ወቅት የደህንነት ቀበቶ አለማሰር፣ የቴክኒክ ምርመራ ቦሎ አለማደስ፣ 3ኛ ወገን አለመግባት፣ ትርፍ ተሳፋሪ መጫን፣ ያልተፈቀደ እስቲከር መለጠፍ፣ ያለ መንጃ ፍቃድ ማሽከርከር እንዲሁም በተለያዩ ደንብ መተላለፎች ላይ ያተኮረ የቁጥጥር ሥራ ተሰርቷል::

በዕለቱ በተሰራው የቁጥጥር ሥራ  በአጠቃላይ 431 ተሽከርካሪዎች የታዩ   ሲሆን፡  ከነዚህ ውስጥ ደንብ ተላልፈው የተገኙ 56 አሽከርካሪዎች  ላይ  ተገቢው የህግ ማስከበር እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ ታውቋል:: ከደንብ ተላላፊዎች  ብር 57,500 (ሃምሳ ሰባት ሺ  አምስት መቶ  ብር) ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በቁጥጥር ወቅት የተወሰነ ክፍተት ያለባቸው አሽከርካሪዎች 375 የሚሆኑት በቀጣይ እንዲያስተካክሉ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት 850 ለሚሆኑ ተሳፋሪዎችና ለ100 ባለ 2 እግር ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችን ጨምሮ ግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ተሰርቷል:: የተቀናጀው ቡድን የቁጥጥር ሥራ በቀሪ ቀናት በተለዩ ቦታዎች ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

24/03/2017 ዓ.ም

ሐዋሳ፥ ሲዳማ

newz 1001

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም ከመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ የተውጣጣ ግብረ ሀይል የድጋፍና ቁጥጥር ሥምሪት እንደተሰጠው ተመላከተ።

የድጋፍና ቁጥጥር ተልዕኮው የሚተገበረው በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማና በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ሲሆን ለ12 ቀናት እንደሚቆይም ተብራርቷል።

የቢሮ ሀላፊው አቶ ታምሩ ታፌ ሥምሪቱን ለግብረ- ሀይሉ ሲሰጡ በንግግራቸው:- ተልዕኳችሁ በዋናነት በመናኽሪያዎች አካባቢ የሚካሄድ የህግና ደንብ ትግበራ በተጨማሪም በእንቅስቃሴ ወቅት አሽከርካሪዎች ደንብና ህግ ጠብቀው ስለመንቀሳቀሳቸው ትኩረት ሠጥተው እንዲሰሩ  አስገንዝበዋል።

አክለውም ተልዕኳችሁ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ተቋማችን ከጎናችሁ ነው ሲሉ አብሮነታቸውን አረጋግጠዋል።

ለተቀናጀ ቁጥጥር ሥራ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ እና የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስቧል::

የከተማ ታክሲ ታሪፍ ጥናት ተሰርቶ በሀዋሳ እና በክልል ከተሞች ተግባራዊ እንዲደረግ በቢሮ በኩል የወረዳውን ተግባራዊነቱ በግብረ ኃይሉ በኩል በትኩረት ጠንካራ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ አስገንዝቧል::

18/03/2017 ዓ.ም.

ሐዋሳ ሲዳማ

newz001

Doogote Latishshinna Hodhishshu Biiro mootimmate loosaasinera "Ajuujate wolqa luphiima lophora" yaanno birxichinni qajeelsha aa hananfoonni.

Doogote Latishshinna Hodhishshu Biiro mootimmate loosaasinera "Ajuujate wolqa luphiima lophora" yaanno birxichinni qajeelsha aa hananfoonni.

Qajeelshu battala faajetenni faninohu Biirote sooreessi kalaa Taamiru Taffehu isi widoonni sokkasi sayisanni gobbate deerinni mootimmate loosaasinera uyinnanni qajeelsha ikkasinni yanna'nsa garunni horo'nsidhe gobbate gede loonsanni hee'noonni loossanna aantete amandoonni illacha garunni huwata hasiisanota xawisino.

Biirote qajeeltino wolqa kalanqanni gobbate gedeno ikko Qoqqowu deerinni paartetenna mootimmate loossa lifinxetenninna gumaamimmatenni gumulantano gede assate aantetenno illacha tunge loonsannita xawinsoonni.

Qajeelshu battala qixaabbe shiqino sanade nabbawatenni hana'nfoonniha ikkanna lamu barirrano keeshitanota xawinsoonni.

Bocaasa, 02/2017, Hawaasa

bhead

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

ተቀናጅቶ መሥራት ለሴክተር ሥራ መሳካት ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ::

bhead

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሴክተር ጉባኤ ተካሂዷል::

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ አስፋው ጎኔሶ እንደገለፁት ይህ ሴክተር ለሲዳማ ሕዝብ የመልማት ቁጥር አንድ አጀንዳ የሆነውን የመንገድ የልማት ሥራን የሚሰራ ተቋም በመሆኑ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው መስራት ያስፈልጋል ብለዋል::

የመንገድ እና የድልድይ ግንባታ ተደራሽነት እንደ ጥሩ የሚታይ ቢሆንም ከጥራት ጋር ተያይዞ ለሚታዩ ችግሮች ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንደሚገባ ተገልጿል::

በሌላም በኩል የትራንስፖርት ዘርፍ አከባቢ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋና በቴክኖሎጂ የተደገፈ በማድረግ የሕዝቡን እንግልት ማስቀረት እና የትራፊክ ቁጥጥር ሥራዎችን ሪፎርም በማድረግ የሚታዩ ችግሮች ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ይገባል በማለት ተናግሯል::

በመክፈቻው ወቅት የቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ታምሩ ታፌ እንደተናገሩት በቢሮ ደረጃ በመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራዎች በበጀት ዓመቱ ዉጤታማ እንደነበረ ተናግረዋል::

በመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍም በተሰራው ሥራ የሞት መጠን የቀነሰ ቢሆንም  በሰው እና ንብረት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ማስቆም እስካልቻልን ድረስ በመቀናጀት መስራት እንደሚገባ ተጠቅሷል::

በክልል ደረጃ በ2016 በጀት ዓመት 107  የሞት አደጋ መከሰቱንና ከፍተኛ የንብረት ውድመት እና የአካል ጉዳት የደረሰ በመሆኑ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በሙሉ  በመቀናጀት የአደጋ መንስኤን በመለየት መስራትና መከላከል እንደሚገባ ተገልጿል::

በሴክተር ጉባኤው ለዉይይት መነሻ የሆኑ ሰነዶች የ2016 በጀት ዓመት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድን የቢሮው የልማት እቅድ በጀት ክትትል ዳይረክቶሬት ዳይረክተር አቶ ወገኔ ታምራት ያቀረቡ ሲሆን የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላከያ የንቅናቄ ሠነድን ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ዘርፍ ኃላፊ አቅርበው ውይይት ተደርጓል::

rd

የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመከላከል እና አደጋዉን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ ተቋማት እና አካላት በመቀናጀት ከሰሩ የንቅናቄ ሠነዱን ሲያቀርቡ ኮሮኔል ሮዳሞ ኪአ ተናግረዋል::

በመድረኩም የተሻሻለው የትራፊክ ቅጣት ደንብ እና በአደጋ ወቅት የመጀመሪያ ሕክምና ክፍያ ማሻሽያ የተደረገውን ደንብ እስከታች በመውሰድ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ በቀረበው ሠነድ ተብራርቷል::

በመጨረሻም በቀረቡት ሰነዶች ላይ ከተሳታፊ አካላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥተው በቀጣይ በሴከተር ደረጃ በቅንጅት በመስራት የተጣሉ ግቦችን ማሳካት አስፈላግ መሆኑን ገልፆዎ ከዞኖች እና ከሐዋሳ ከተማ አስተዳር ጋር በቀጣይ በምሰሩ አቅጣጫዎች ላይ የግቢ ስምምነት ተደርጎ የሴክተር ጉባኤ መድረክ ማጠቃለያ ተደርጓል::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አስፋው ጎኔሶ፣የቢሮ ኃላፊ ክቡር ታምሩ ታፌ፣ የፕሬዘደንቱ የመሰረተ ልማት አማካሪ ክቡር ዘገዬ ሀሜሶ፣ ክብርት ምንትዋብ ገ/መስቀል የከተማ እና መሰረተ ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የዞንና የሐዋሳ ከተማ አመራሮች፣የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የባለድርሻ አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

   =======================

መስከረም, 2017 ዓ.ም

Hawaasa, Sidaama

rod

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

rod

ይህ የተገለፀዉ ለአሽከርካሪዎች በሥነ- ምግባር፣ አዲስ በተሻሻሉ የመንገድ ደህንነት ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የመድህን ፈንድ አዋጆችን ለማሳወቅ በተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው።

በመድረኩ በርካታ አሽከርካሪዎች፣ የትራፊክ ፖሊስ አባላት፣ የክልልና መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች  ተሣታፊ ሆነዋል።

road safety 2
road safety 3

የቢሮ ሀላፊ ተወካይና የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ሀላፊ ኮ/ ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የዛሬው መድረክ ዓላማ አሽከርካሪዎች የተከበረ ሙያ ያላችሁ የተከበረውን የሰው ልጅን ህይወት ይዛችሁ የምትንቀሳቀሱ፣ በስነምግባር የታነፃችሁና አዳዲስ ከወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር እንድትተዋወቁ ታሳቢ በማድረግ ነው።

 አክለዉም ባለፈው ዓመት በተከሰተው የትራፊክ አደጋ ዋናው መንስዔ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን ገልፀው በዝግታና በእርጋታ እንድታሽከረክሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሰነዶች ቀርበው በሳል ሙያዊ ገለፃ ተደርጎባቸዋል።

road safety

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አዳነ አየለና የክልሉ መንገድ ደህ/አቅ/ግን/ድህ /አደ/መድህን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ዶካ ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተውባቸው መግባባት ላይ ተደርሶ  መድረኩ ተጠናቋል።

 “በትራፊክ አደጋ አንድም ህይወት እንዳይጠፋ፣ አካል እንዳይጎድል፣ ንብረት እንዳይወድም ሁላችንም ሀላፊነት አለብን! “

 መስከረም 2017 ዓ.ም

Hawaasa, Sidaama

nez1

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላክያ የአብይ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የመንገድ ትራፊክ አደጋ መከላክያ የአብይ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ::

በመድረኩም የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር በየነ ባራሳ, የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ታፌ የኮሚቴ አባላት የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

በመድረኩም አጠቃላይ ክልላዊ የትራፊክ አደጋ መከላክያ የመነሻ ሠነድ በቢሮ ኃላፊ በአቶ ታምሩ ታፌ ቀርቦ የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት በማድረግ በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል እንደሆነ በማንሳት ሁሉም እንደ ተቋማቸው ወስደው የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚሰሩ ገልፀዋል::

በተጨማሪም በክልል ደረጃ እንዲሁም በሁሉም ዞኖች እንዲሁም በወረዳዎች የግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስቷል::

የትራፊክ አደጋ እንዴ ሀገር እያደረሰ ያለዉን ዘርፈ ብዙ ጉዳትን ለመቀነስ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ እንዲሰሩ ለማድረግ ታቅዶ የተዘጋጀ መድረክ ሲሆን በአስከፍው የመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት የሞት የአካል ጉዳት እንዲሁም በእኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ እያደረሰ ያለውን ቀውስን ለመቀነስ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ተገልፆዋል::

በመጨረሻም ክቡር ምክትል ፕረዝደንት እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ በቀጣይ ከኮሚቴ ምስረ ታ ጀምሮ በክልል ደረጃ በሚሰሩ ስራዎች ላይ በቅርበት በቅንጅት በመሥራት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ የድርሻቸውን እንዲወጡ እና ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አቅጣጫ ተቀምጧል::

ሰኔ 03/2016 ዓ.ም
Hawaasa, Sidaama

newz199

Ayirradu Kalaa Taamiru Taaffehu Doogote Latishshinna Hodhishshu Biiro sooreessi "mootimmate loosaasine umikki yanna qoqqowu deerrinni sekterrate heewora qeelletenni sa'anke korkaatta assatenni hawalle hagiidhinummo" yitanno sokka saayisino.

Ayirradu Kalaa Taamiru Taaffehu Doogote Latishshinna Hodhishshu Biiro sooreessi "mootimmate loosaasine umikki yanna qoqqowu deerrinni sekterrate heewora qeelletenni sa'anke korkaatta assatenni hawalle hagiidhinummo" yitanno sokka saayisino.

Beeddahe Hawaasira iimaanni balka yite xabbu.

Uurrinshanke sokka jeefisatenna woyyino guma borreessiisate gutunna mittimmate sewo hedotenna loosu mittimma ajjino yanna giddo ijaarsatenni mootimmate uurrinsha lekkate kaase ispoortete heewora hananfoommoha labballunna seennunni abbinoommo shaapeene woy qeelle giddo sekterenke kaajjillenna laanfe bande kaajjillu lede haranno assatenni, laanfe noowa kaayinni yanna uynikkinni taashshine bilchaantetenni hanfoommo harinsho qaafo leellishanno guma ikkinota buunxoommota techo hee'noommori naqaashshete.

Ikkinohura, tini qeelle aantete duuchunku handaarinna dayroktereetete hattono ogeeyyenkenna xaphooma tantanonkera uynoommo baaychinni irkisamatenni qinaambenne xambe kalanqe mooranna baincho assote xawoho sharramme dagankera taalleenyunna sumbetenni uynoonninke yannanni owaantete kasseenya buuxisiinsummoro loosonke xawoho keenne hasiisannonke guma uysiisannonkenna baatinonke magani, mootimma, paartetenna daganke albaanni woxunnu hidha dandiinannikki waaginni hendanniha naqaashshete baraa'rsha xawoho dagate mereero adha saino ayirrinyinna kasso may no?

Sekterenkera baayriidiri hattono baxeemmo'nenna ayirriseemmo'ne miillanna maate'ya, konnira gattino yanna anninke kaaliiqi irkonna halesinna eltosi baalunku aleenni mittimmate agarooshshe batiseennanke uynonke keerinna mittimmanni fulanno baxillenna shaqqille uddi'ne hedote mittimmanni amadamme agarennanke woyyino guma borreessiinse roorino afansha kaaysate eeggo yaanni, baayiriidinna muxxe ikkitinoonni godo'laanonna loosaasinenke hattono xaphooma ispoortete maate daafuri'nera qeelle hasiissannohura ki'nenni naaxxinoommona hawalle tashshi yii'ne yeemmo.

Jeefoteno, gumulonke qeellete boowenni dukkisante Hawaasira iimaanni hagiirrinke xawanno gede bobbakkinoonniri baalunku hanafo'ne harinshonna gumulo'ne mittimmatenni gutu qeellera kaajjado ispoortete ayyaani hagiirunna sewotenni hattono baxillunni balka yeenna guggushamino gumanna qeellera fultinanniha ikka'nera halcheemmo.

Dancha yanna!

Badheessa 22/2016 M.D.

Hawaasa, Sidaama

newz112

Qinaawinoha Doogote Tiraafikete Qorqorshanna hedo cu'mishiishate looso badheessa 9-25/2016 M.D geeshsha uynannita xawinsi.

Qinaawinoha Doogote Tiraafikete Qorqorshanna hedo cu'mishiishate looso badheessa 9-25/2016 M.D geeshsha uynannita xawinsi.

Doogote Tiraafikete korkaattinni mannunna jajju aana iillitanno tiraafikete dano afamino garinni agishate qinaawote doogote keeraanchimma qorqorsha hedo cu'mishiishate loosi Sidaamu Qoqqowi badheessa 9-25/2016 M.D uyinannita sidaamu qoqqowi doogote latishshinna hodhishshu biiro sooreessi ayirradu Kalaa Taammiru Taffehu Midiyaho gaazeexaawe xawishsha uyno.

Kalaa Taammiru Taffehu xawishshisinni wodhote laise qorqorsha assitanno bissaranna oofaanote hedo cu'mishiishate qineessatenni irkisatenna harunsatenni hattono qorqoratenni higge ayirrisiisate looso xa'mamooshshu noo garinni harisate lamu goommi motore owaante aate kaajjado hedo cu'mishiishatenna qorqorshu looso kaajjishate qoqqowu loosu sooreeyye,hodhishshu qorqoraano, Tiraafikete miilla ledo noo qinaawote loossa kaajjishatenna addinta busha ikkitino doogote tiraafikete dano ajishate ikkinota xawishshisinni huwachishino

Qinaawotenni doogote tiraafikete qorqorshanna hedo cu'mishiishate looso doogote keeraanchimmanna mediini fendete owaante qineessaanchimmanni federaalete polisete komishiine sidaamu qoqqowi doogote latishshinna hodhishshu biiro hattono sidaamu qoqqowi xaphooma plisete biddishshi ledo halamatenni loonsanni looso ikkanno.

Pirogiraamete garinni oofaanotenna rosaanote tiraafikete kiwabba komitera uyinannihu hedo cu'mishiishate qajeelshi Hawaasi Quchumira, Hirgaalemete quchumira hattono Alatta wondi quchumu gashshootira uynanniha ikkasi xawishsha uynini yannara huwachinshoonni.

Qinaawotenni doogote tiraafikete qorqorshanna hedote looso sidaamu qoqqowi Hawaasi quchumi gashshootinni kaayinse soojjaati zoone Bansi quchumi geeshsha doorroonni doogga aana loonsanniha ikkanno.

Badheessa 8/2016 M.D

Hawaasa, Sidaama