በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

በሲዳማ ክልል ሀገራዊ የተቀናጀ መንገድ ደህንነትና ትራፊክ ቁጥጥር ሥራ ተጀመረ ::

ከፌዴራል መንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት፣ ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም ከመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ የተውጣጣ ግብረ ሀይል የድጋፍና ቁጥጥር ሥምሪት እንደተሰጠው ተመላከተ።

የድጋፍና ቁጥጥር ተልዕኮው የሚተገበረው በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማና በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ሲሆን ለ12 ቀናት እንደሚቆይም ተብራርቷል።

የቢሮ ሀላፊው አቶ ታምሩ ታፌ ሥምሪቱን ለግብረ- ሀይሉ ሲሰጡ በንግግራቸው:- ተልዕኳችሁ በዋናነት በመናኽሪያዎች አካባቢ የሚካሄድ የህግና ደንብ ትግበራ በተጨማሪም በእንቅስቃሴ ወቅት አሽከርካሪዎች ደንብና ህግ ጠብቀው ስለመንቀሳቀሳቸው ትኩረት ሠጥተው እንዲሰሩ  አስገንዝበዋል።

አክለውም ተልዕኳችሁ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ተቋማችን ከጎናችሁ ነው ሲሉ አብሮነታቸውን አረጋግጠዋል።

ለተቀናጀ ቁጥጥር ሥራ ሁሉም የባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ እና የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስቧል::

የከተማ ታክሲ ታሪፍ ጥናት ተሰርቶ በሀዋሳ እና በክልል ከተሞች ተግባራዊ እንዲደረግ በቢሮ በኩል የወረዳውን ተግባራዊነቱ በግብረ ኃይሉ በኩል በትኩረት ጠንካራ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ የቢሮ ኃላፊ ጨምሮ አስገንዝቧል::

18/03/2017 ዓ.ም.

ሐዋሳ ሲዳማ

Tenne Odoo Iillishshe

Comments are closed.