ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ወቅቱን የጠበቀ የሙያ ላይ ሥልጠና ግንዛቤን የማሳደግ አቅሙ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

rod

ይህ የተገለፀዉ ለአሽከርካሪዎች በሥነ- ምግባር፣ አዲስ በተሻሻሉ የመንገድ ደህንነት ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የመድህን ፈንድ አዋጆችን ለማሳወቅ በተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው።

በመድረኩ በርካታ አሽከርካሪዎች፣ የትራፊክ ፖሊስ አባላት፣ የክልልና መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች  ተሣታፊ ሆነዋል።

road safety 2
road safety 3

የቢሮ ሀላፊ ተወካይና የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት ዘርፍ ሀላፊ ኮ/ ሮዳሞ ኪአ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የዛሬው መድረክ ዓላማ አሽከርካሪዎች የተከበረ ሙያ ያላችሁ የተከበረውን የሰው ልጅን ህይወት ይዛችሁ የምትንቀሳቀሱ፣ በስነምግባር የታነፃችሁና አዳዲስ ከወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር እንድትተዋወቁ ታሳቢ በማድረግ ነው።

 አክለዉም ባለፈው ዓመት በተከሰተው የትራፊክ አደጋ ዋናው መንስዔ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን ገልፀው በዝግታና በእርጋታ እንድታሽከረክሩ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሰነዶች ቀርበው በሳል ሙያዊ ገለፃ ተደርጎባቸዋል።

road safety

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ አቶ አዳነ አየለና የክልሉ መንገድ ደህ/አቅ/ግን/ድህ /አደ/መድህን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ዶካ ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተውባቸው መግባባት ላይ ተደርሶ  መድረኩ ተጠናቋል።

 “በትራፊክ አደጋ አንድም ህይወት እንዳይጠፋ፣ አካል እንዳይጎድል፣ ንብረት እንዳይወድም ሁላችንም ሀላፊነት አለብን! “

 መስከረም 2017 ዓ.ም

Hawaasa, Sidaama

Tenne Odoo Iillishshe

Comments are closed.