በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ድጋፍ እና ክትትል ግብረ መልስ ተሰጠ፡፡

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ድጋፍ እና ክትትል ግብረ መልስ ተሰጠ፡፡

በበጀት ዓመቱ በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የመንገድ እና ድልድይ ግንባታ መሰረተ ልማትን ለማፋጠን ትኩረት ተሰጥተዉ እየተሰራ የቆየ ሲሆን በመንግስት በጀት ብቻ በየዓመቱ በጀት ተይዞ የማህበረሰቡን የመንገድ ጥያቄዎችን መመለስ አስቸጋር በመሆኑ ህበረተሰቡን በማሳተፍ የመንገድ እና የድልድይ ግንባታ ሥራዎች በሁሉም ወረዳዎች እንዲከናወኑ ተደርጓል፡፡

በዚህም በዓመቱ ለማከናወን ዕቅድ ከተያዙ አዳዲስ የመንገድ ከፈታ እና የጥገና ስራዎች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ከመንግስት በጀት ዉጪ ህበረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደተቻለ ለዞኖች በዓመቱ የተከናወኑ ሥራዎችን መነሻ በማድረግ ግበረ መልስ በተሰጠበት ወቅት ተገልጿል፡፡

በደቡባዊ ሲዳማ ዞን ደረጃ ህበረተሰቡን በማሳተፍ በተሰራው ስራ በሁሉም  ወረዳዎች አደረጃጀቶችን እስከ ቀበሌ ድረስ በመጠቀም በሁሉም ቀበሌያት በልማት ቡድን ንቅናቄ ተደርጎ በተሰራዉ ሥራ ማህበረሰቡ ተጠቃሚ መሆን መቻሉን በተሰጠው ግብረ መልስ በተሰጠበት ወቅት ተገልጿል:: 

በዞን ደረጃ ከቢሮ ጋር በመቀናጀት እስከታችኛዉ መዋቅር ድረስ እቅድ በማዉረድ እንዲተገበር ለማድረግ በተቀመጠዉ እስታንዳርድ መሰረት ከ6-8 ሜትር  ድረስ እንዲሰራ መግባባት ላይ ተደርሶ የከፈታ እና ጥገና ሥራ ማከናወን መቻሉን  ተገልጿል፡፡

የወጣውን የመንገድ እሰታንዳርድ መነሻ ከማከናወን አንጻር በአንዳንድ ወረዳዎች ላይ ጉድለቶች መታየቸውን እና እቅዱን በሁሉም ቀበሌ  ተደራሸ አለማድግ፤ ከእስታንዳርድ በታች የመንገደ ከፈታ ማከናወን እና መንደርን ከመንደር ከማገናኝት ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ማረም እንደሚገባ እና በቀጣይ በጀት ዓመት ማረም የሚገባቸው እንደሆነ ተብራርቷል፡፡

በግበረ መልሱ መድረክ ላይ የደቡባዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳር  አቶ መንገሻ ፊታሞ የመንገድ ልማት እና ትራንስፖርት ቢሮ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ህብረት ቢያ የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የወረዳ አመራሮች ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል ፡፡

ስኔ 18/2017 ዓ.ም 

ሀዋሳ፣ሲዳማ

Tenne Odoo Iillishshe

Comments are closed.